ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወንድማማች አፀደ ሕፃናትና የመ/ደ/ት/ቤት በ2018 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውል ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ለሁለተኛ ዙር የወጣ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወንድማማች አፀደ ሕፃናትና የመ/ደ/ት/ቤት በ2018 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውል ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
- የትምህርት እቃዎች
- የደንብ ልብስ
- ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች
- አላቂ የፅዳት እቃዎች
- ቆሎ እና ኩኪስ
- የደንብ ልብስ ማሰፊያ
በዚህ መሠረት በጨረታው መሣተፍ ለሚፈልጉ፡-
- በዘርፉ የተሰማሩ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የዘመኑን ግብር አጠናቀው የከፈሉ ለዚህም ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- በተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ፣ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ለጨረታ ማስከበሪያ የሚውል የሚመለስ በባንክ በተረጋገጠ CPO ብር 1000 /አንድ ሺ ብር/ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ለጨረታ ሰነድ ለእያንዳንዱ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ የማይመለስ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 /አስር / ተከታታይ የሥራ ቀናት በወንድማማች የመ/ደ/ት/ቤት ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 4 በግንባር በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዕቃ ናሙና ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማቅረብ ይኖርባቸዋል ናሙናውን ካላቀረቡ ግን ጨረታው ውድቅ ይሆናል፡፡
- የጨረታው ሰነዱ ኮፒና ኦርጅናሉ ብሎ በመለየት በታሸገ ኢንቨሎፕ በተለያዩ ፖስታ አሸገው ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ ዝርዝር ሰነድ ላይ ባለው ማቅረቢያ ቦታ በግልፅ ሞልተው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ እስከ 10 /አስር/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ለዚህ በተዘጋጀው ሣጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ የሚከፈተው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው በወጣበት በ10ኛው ቀን 11 ሰዓት ተዘግቶ በማግስቱ በ4፡45 ሰዓት በት/ቤቱ የሰው ኃይል ቢሮ ይከፈታል እለቱ በዓል ከሆነ በቀጣዩ ቀን ይሆናል፡፡
- የጨረታው አሸናፊው ያሸነፈበትን ዕቃ የጠቅላላ ዋጋውን 10% ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ ቼክ /CPO/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ዋጋ ሲያቀርቡ እስከ ቫቱ እንዲያቀርቡ፡፡
- አነስተኛና ጥቃቅን የተደራጃችሁ አቅራቢዎች ካላችሁበት ወረዳ የዋስትና ደብዳቤ ማምጣት አለባችሁ፡፡
- ት/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መበቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ ማብራሪያ፡-
አድራሻ፡- ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 11 ቡልጋሪያ ከቀድሞው በግ ተራ ወደ ውስጥ ገባ ብሎ ቢይ ሜዳ ኮንዶሚኒየም አጠገብ
የስልክ ቁጥር፡- 0114164212/0114705897
የመ/ሣ/ቁ፡- 6388 አዲስ አበባ
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወንድማማች አፀደ ሕፃናትና የመ/ደ/ት/ቤት
