የጥቁር ዓባይ ኮንስትራክሽን አ/ማህበር (በሕግ በመፍረስ ላይ ያለ) በአዲስ አበባ ሣሪስ ማዕከላዊ ጋራዥ ግቢ ውስጥ የሚገኙትን ተሽከርካሪ፣ የተለያዩ መለዋወጫ ዕቃዎች እና ሌሎች የተለያዩ ንብረቶችን እንዲሁም አቃቂ ጠጠር ማምረቻ የሚገኙ ዛፎችን ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ተሽከርካሪ የተለያዩ የመለዋወጫ ዕቃዎችና ሌሎች የተለያዩ ንብረቶች፤ ለመሸጥ የወጣ ጨረታ ቁጥር 01/2018
የጥቁር ዓባይ ኮንስትራክሽን አ/ማህበር (በሕግ በመፍረስ ላይ ያለ) በአዲስ አበባ ሣሪስ ማዕከላዊ ጋራዥ ግቢ ውስጥ የሚገኙትን ተሽከርካሪ፣ የተለያዩ መለዋወጫ ዕቃዎች እና ሌሎች የተለያዩ ንብረቶችን እንዲሁም አቃቂ ጠጠር ማምረቻ የሚገኙ ዛፎችን ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም፡-
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ) በመክፈል ሳሪስ ንፋስ ስልክ ቀለም ፋብሪካ አጠገብ ከሚገኘው አ/ማህበሩ ቢሮ የጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ንብረቶች የጨረታ ሰነድ በመያዝ ዘወትር በሥራ ሰዓት የሚሰጠውን የመግቢያ ወረቀት በመያዝ ንብረቶቹ ባሉበት መመልከት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ ከሚጫረቱበት ጠቅላላ ዋጋ አስር በመቶ (10%) በባንከ በተመሰከረለት ቼክ (ሲ.ፒ.ኦ) በድርጅቱ ትክክለኛ ስም BLUE NILE CONSTRUCTION SHARE COMPANY በማሰራትና ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ በፖስታው ላይ የተጫራቹን ስምና አድራሻ በግልፅ በመፃፍ እስከ ጨረታው መዝጊያ ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- በቂ የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) ያላስያዙ ተጫራቾችን ኮሚቴው ከጨረታው ሊሰረዝ ይችላል።
- የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያው አሸናፊዎች የጨረታው ውጤት እንደፀደቀ ተመላሽ የሚደረግ ሲሆን ለአሸናፊዎች ግን የገዙበትን ዋጋ አጠቃለው ከከፈሉ በኋላ ይሆናል።
- የጨረታው አሸናፊዎች ውጤቱ በተገለፀ በ10 /አስር/ ቀናት ውስጥ ከፍያ በመፈፀም ያሸነፉባቸውን ንብረቶች በ15 ቀናት ውስጥ አንስተው ማጠናቀቅ አለባቸው፣ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሳያነሱ ቢቀሩ ለሚፈጠረው ችግር መ/ቤቱ ተጠያቂ አይሆንም፣
- ከላይ በተጠቀሰው 15 ቀናት ውስጥ ንብረቱን አጠናቆ ያልወሰደ (ያላነሳ) ተጫራች የመጋዘን ኪራይ በቀን ብር 100 (አንድ መቶ) እንዲከፍል ይደረጋል፡፡
- አክሲዮን ማህበሩ ያወጣውን የጨረታ ሰነድ በስሙ ሳይገዛ የተወዳደረ ማንኛውም ተጫራች ከውድድሩ ውድቅ ይደረጋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአ/ማህበሩ ቢሮ ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ4፡00 ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ በ4:30 ይከፈታል፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ስልክ ቁጥር- 011 442 63 32
የጥቁር ዓባይ ኮንስትራክሽን አ/ማህበር
