በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ስር የሚገኘው የወረዳ 11 ጤና ጣቢያ የሚከተሉትን እቃዎችና ስራዎች በ2ኛ ዙር ን/ሰ/ወ11/02/2018 ዓ.ም ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ስር የሚገኘው የወረዳ 11 ጤና ጣቢያ የሚከተሉትን እቃዎችና ስራዎች በ2ኛ ዙር ን/ሰ/ወ11/02/2018 ዓ.ም ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
እነሱም፡ የደንብ ልብስ፤ አላቂ እቃ፤ የአገልግሎት ግዥ (የመኪና ጭነት)፤ የጥገና እቃዎች እና ስራ፤ የህትመት ስራ፤ ቋሚ እቃዎች፤ ሻይ ቡና፤ የተለያዩ የህክምና እቃዎች እና መድሀኒቶች፤ የጽዳት እቃ፤ የደንብ ልብስ ስፌት መግዛት ይፈልጋል፡፡ ሆኖም ተጫራቾች እቃው በእስቶር ውስጥ ስለመኖሩ ወይም የቴክኒክ ባለሙያዎች መተው ማየት ሲፈልጉ እንደሚያቀርቡ ማረጋገጫ ደብዳቤ መስጠት የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡ ሆኖም ግን የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ በጨረታ ላይ መሳተፍ ትችላላችሁ።
- ተጫራቾች አግባብ ያለዉ የዘመኑ ግብር የተከፈለበት እና የታደሰ ንግድ ስራ ፍቃድ፣
- በመንግስት ግዢ እና ንብረት አሰተዳደር ኤጀንሲ የእቃ አቅራቢዎች ዝርዝር ሊስት ላይ የተመዘገቡ እና በጨረታ ለመሳተፍ የሚችል ድብዳቤ ማቅረብ የሚችል፡
- የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ቫት/ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እና የግብር ከፋይነት የምስክር ወረቀት እንዲሁም ለጥቃቅን እና አነስተኛ ከአደራጃቸዉ አካል ድብዳቤ እና ድበዳቤው ሼድ እንዳላቸዉ የሚገልጽ መሆኑን አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ለሚወዳደሩበት ለእያንዳንዱ ሎት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 (አስር) የሥራ ቀናት ውስጥ አራተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 409 ዘወትር በስራ ሰዓት 400.00 (አራት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይኖርባችኋል፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የእቃ ዝርዝርና ዋጋ እና መለያ ቁጥር ከላይ ከተጠቀሰዉ ተራ ቁጥር 1 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ማህተምና ፊርማ በማኖር ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት የጨረታውን ሰነድ አራተኛ ፎቅ በግዥ ቡድን መሪ ቢሮ ውስጥ ባለው በታሸገ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- በመክፈቻ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች ያለመገኘት የጨረታውን ሳጥን መክፈቻ ስነስርዓት አያስቀርም፡፡
- ፋይናንሻል እና እንዲሁም ቴክኒካል ኦሪጀናል ብሎ በመለየት በአንድ ፖሰታ በማሸግ ፊርማ እና ማሀትም በማድረግ ማስገባት አለባቸው።
- የጨረታ ማስከበሪያ፡- የግዥውን 1(15,000) (አስራ አምስት ሺህ ብር ብቻ)
- የጨረታ ሳጥን በአስረኛው ቀን ከቀኑ 11፡30 ሰዓት ታሽጎ በሚቀጥለው የስራ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከቀኑ 4፡00 ሰዓት በጤና ጣቢያው ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ናሙና ለሚያስፈልጋቸው እቃዎች ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል መ/ቤቱ ናሙና ራሱ አቅርቦ ዕጩ ተወዳዳሪዎች ለእይታ አስቀርቦ በናሙና መሰረት እንዲያቀርቡ የሚያደርጋቸው ግዥዎች መኖራችው እንዲታወቅ፡፡ የሚቀርቡ ናሙናዎች ብዛት በዋጋ ሰነድ ላይ ይመልከቱ የሚቀርቡበት ጊዜ ጨረታ ከመከፈቱ በፊት ሲሆን የሚቅርቡት ክፍል ራሱ በተዘጋጀዉ ክፍል ነው።
- ተጫራቾች ያቀረቡት ናሙና በሚመረመርበት ወቅት በእቃዉ ባህሪ ምክንያት ቢበላሽ ቢጠፋ ካሳ አይከፈልም። ዉጤት ከተገለጸበት ቀን አንሰቶ በ6 ወር ውስጥ ካልወሰዱ በዉርስ ለመንግስት ገቢ ይሆናል፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጫረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- መደበኛ የጨረታ ሰነድ (SBD) ከተቋሙ የተወሰዱትን አንብቦ እና የተሞላ አድርጎ ሙሉ በሙሉ የጨረታ ሰነዱን መመለስ /ማስገባት/ ይኖርባቸዋል፡፡
የመስሪያ ቤቱ አድራሻ
ን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ወረዳ 11 ጤና ጣቢያ ልዩ ስም ሀና ማሪያም ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፊት ለፊት፡፡
ለበለጠ መረጃ:- የስልክ ቁጥር፡-011-47-119-74
በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ የወረዳ 11 ጤና ጣቢያ
