የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመ/ቤቱ ቅርንጫፍ በሆነው በቃሊቲ እቃ ግ/ቤት ውስጥ የተከማቹትን ልዩ ልዩ ያገለገሉ የቢሮ መገልገያ ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር T- 01/2018
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመ/ቤቱ ቅርንጫፍ በሆነው በቃሊቲ እቃ ግ/ቤት ውስጥ የተከማቹትን ልዩ ልዩ ያገለገሉ የቢሮ መገልገያ ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሰረት ተጫራቾች
1. በጨረታው ለመሳተፍ ፍላጎት ያለው ማንኛውም ግለሰብ ወይም ድርጅት የጨረታውን ሰነድ ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ብር 30.00 ወይም በኢትዮጵያ ውስጥ ሊመነዘር በሚችል ተመጣጣኝ ሌላ ገንዘብ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቁጥር 1000002579859 ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ስም በማስገባትና በአስተዳደሩ ዋና መ/ቤት 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 105 በመቅረብ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ መግዛት ይችላሉ፡፡
2. ተጫራቾች ላገለገሉ ንብረቶቹን በቃሊቲ እቃ ግ/ቤት በሚገኙ የመ/ቤቱ ቅርንጫፎች በአካል በመሄድ መመልከት ይችላሉ፡፡
3. የጨረታው አሸናፊ የሚወሰነው በጨረታ ሰነዱ ውስጥ በተመለከቱት መስፈርቶች መሠረት ሲሆን ጨረታው ዜግነትን ሳይመለከት ለማንኛውም በዚህ ሥራ ላይ ለተሰማራ ክፍት ነው። የጨረታ ሰነዱ የተዘጋጀው በአማርኛ ቋንቋ ነው፡፡
4. ተጫራቾች ጨረታቸውን ለዚህ ተግባር በተዘጋጀ ሳጥን ቢሮ ቁጥር 105 ገቢ የሚያስገቡት የመጨረሻ ቀን የካቲት 18 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጠዋቱ 4:00 ሰዓት ድረስ ብቻ ነው፡፡
5. ጨረታው ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የካቲት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት በመ/ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
6. ተጫራቾች ለሚገዙት ላገለገሉ ንብረት የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ብር 5,000.00 (አምስት ሺ ብር) በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ስም አሰርተው ከመጫረቻ ሰነዱ ጋር በማያያዝ ሳጥኑ ውስጥ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
7. ተጫራቾች በጨረታው ደንብና መመሪያ መሰረት ጨረታቸውን ማቅረብ አለባቸው፡፡ ከጨረታው ደንብና መመሪያ ውጭ የሚቀርብ ማንኛውም ጨረታ ተቀባይነት የለውም፡፡
8. መ/ቤቱ ስለ ዕቃዎቹ ሽያጭ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
9. ለበለጠ መረጃ ተጫራቾች የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ፡፡
10. ጨረታው በጋዜጣ የሚወጣበት ቀን ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
የዕቃ ግዥ ቡድን ሁለት
የፖስታ ሣጥን ቁጥር 1770
ስልክ ቁጥር +251 11 558 71 65
ሜክሲኮ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ፊት ለፊት
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
