የየካ ክ/ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የመንግስት ግዥ አስተዳደር ቡድን የ2018 በጀት አመት 3ኛ ዙር የእቃ ግዥ በጨረታ አወዳድሮ ለማከናወን ይፈልጋል።
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 003ኛ ዙር የእቃ ግዥ
የጨረታ ቁጥር 03/2018 ዓ.ም የካ/ዋ/ስ/አ/ጽ/ቤት የመንግስት አስተዳደር በድን
የ2018 በጀት አመት 3ኛ ዙር የእቃ ግዥ
ሎት 1 የተለያዩ የጽህፈት መሣሪያ ግዥ (CPO=10,000)
ሎት 2 የደንብ ልብስ ግዥ (CPO=10,000)
ሎት 3 የአይቲ እቃዎች ግዥ (CPO=10,000)
ሎት 4 ያገለገለ ኤምዲኤፍ ሽያጭ (CPO=10,000)
ሎት 5 LED Screen (6M(H)X3M) (W) ግዥ (CPO=100,000)
ስለዚህ በጨረታ ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ ህጋዊ ተጫራች የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት እንድትጫረቱ ተጋብዘዋል።
1. የታደሰ ንግድ ሰራ ፍቃድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
2. የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
3. የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
4. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢነት እና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ማስረጃ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
5. ተጫራቾች ናሙና እንዲቀርብ የተጠየቁባቸውን ዕቃዎች መጫረቻ ሠነዳቸውን ሲያስገቡ አብረው የተጠየቀውን ወይም የሚወዳደሩበትን ናሙና ማስገባት ግዴታ አለባቸው፡፡
6. የዘመኑ ግብር ስለመክፈላቸው ከሚመለከተው የገቢ ግብር ባለስልጣን ክሊራንስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
7. ተጫራቾች የጨረታ ማሰከሪያ ሲፒኦ ከላይ በተገለፀው መሰረት በአዲስ አበባ ከተማ የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ስም የተዘጋጀ በባንከ ከተረጋገጠ ሲፒኦ ኦርጅናል ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
8. የጨረታ ሰነዱን ሲገዙ የማይመለስ ለእያንዳንዱ ሎት 500 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
9. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በሚገባ በመሙላት ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ኦርጅናል እና ኮፒ መሆኑን በመግለፅ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
10. የጨረታ ሳጥኑ በ11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ እለት ከቀኑ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙ በመንግስት ግዥ አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 9 ውስጥ ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ስርዝ ድልዝ የሌለበት እና ቫትን ያካተተ መሆኑን አለመሆኑን ካልተገለፀ የቀረው ዋጋ ቫት እንደተካተተ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
11. ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ያላሟላ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም
12. ተጫራቾች ጨረታውን ሲያሸንፉ የውል ማስከበሪያ CPO 10% ማስያዝ አለባቸው፡፡
13. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ስልክ ቁጥር፡- 0118 67 8175
የየካ ክ/ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የመንግስት ግዥ አስተዳደር ቡድን
