በሲዳማ ከልላዊ መንግሥት በሀዋሳ ከተማ የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ለ2018 በጀት ዓመት የሚሆን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በሲዳማ ከልላዊ መንግሥት በሀዋሳ ከተማ የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ለ2018 በጀት ዓመት የሚሆን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
· ሎት 1. የኤሌክትሮኒክስ ግዥ
· ሎት 2. የኤሌክትሪክ ዕቃዎች ግዥ
· ሎት 3. ውሃ ዕቃዎች ግዥ
· ሎት 4. ሕንፃ መሣሪያ ግዥ
· ሎት 5. የሞተር ሳይክል ጎማና ባትሪ ግዥ
· ሎት 6. የደንብ ልብስ ግዥ
· ሎት 7. የሞተር ዘይትና ቅባት
· ሎት 8. የኅትመት ግዥ
ተጫራቾች
· ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ ያለው
· የዘመኑን የ2018 ዓ.ም ግብር የከፈሉ፤
· እንደ አስፈላጊነቱ የቫት ተመዝጋቢ የሆነ፤
· በመስክ የንግድ ሥራ የተሰማሩ
የጨረታ ማስከበሪያ በሆስፒታሉ ስም የተሠራ CPO 10,000 (አስር ሺህ ብር) ማስያዝ የሚችሉ፣ የጨረታ ሰነዱ አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ግዥ ከፍል በመቅረብ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡ የጨረታ ሰነድ አንድ አርጅናል ሁለት ኮፒ ለየብቻ ፋይናንሻል እና ቴክኒካል በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በድምሩ 6 ፖስታ ለዚህ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ እንዲያስገቡ ሆኖ በ15ኛው ቀን ከረፋዱ 6፡00 ሰዓት ላይ የጨረታ ማስገቢያ ሳጥን ይታሸግና ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ይህ ቀን ቅዳሜ ወይም እሁድ እንዲሁም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው በሥራ ቀን ይከፈታል፡፡
ማሳሰቢያ
⁕ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙ ጨረታው ተከፍቶ ውሳኔ ይሰጣል፡፡ መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው።
⁕ ፋይናንሻል ሠነድ ከሆስፒታሉ የተዘጋጀው ላይ ብቻ ዋጋ መሙላት ይገባል፡፡
⁕ በፋይናንሻል ሠነድ ላይ የዋጋ መሙያን መቀየርም ሆነ ከተጠየቀው ይዘት ውጪ መለኪያ በመቀየር ዋጋ ሞልቶ ማቅረብ አይቻልም።
ለተጨማሪ መረጃ የስልክ ቁጥር 0462122370
በሲዳማ ክልላዊ መንግሥት በሀዋሳ ከተማ የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል
