Tender Detail

Tender Details


የደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ ሃብት ማመንጨት ኢንተርፕራይዝ መገዘዝ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ ከዚህ በታች በሎት የተጠቀሱትን የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ግብዓት የደንብ ልብስና የንፅህና መጠበቂያ ዕቃዎች ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።


ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

 

የደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ ሃብት ማመንጨት ኢንተርፕራይዝ ዘዝ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ ከዚህ በታች በሎት የተጠቀሱትን የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ግብዓት የደንብ ልብስና የንፅህና መጠበቂያ ዕቃዎች ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

·        ሎት ንድ፡- ለእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ የሚውሉ ግብዓቶች (ፋጉሎ፣ ፍሩሽካ፣ ላየም ስቶን...)

·        ሎት ሁለት፡- የንፅህና መጠበቂያ ዕቃዎች

·        ሎት ሦስት፡ - የደንብ ልብስ (የስራ ልብስ) ዕቃዎች

·        ሎት አራት - የእንቁላል ጣይ ቄብ ዶሮዎች ( 45 ቀን፣ 2 ወርና 3 ወር)

በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ -

1.     ተጫራቾች በዘርፍ የተሰማሩ ሆነው የዘመኑ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሰርተፍኬት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት የንግድ ምዝገባ ምስ ወረቀት የዘመኑን ግብር ፈላቸውን የሚያረጋግጥ ከግብር ሰብሳቢው ባለስልጣን የተሠጠ የምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው፡፡

2.     ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሎት አንድ ብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ ብር) ለሎት ሁለት ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) ለሎት ሦስት ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) እና ለሎት አራት ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) በባንክ በተመሰከረ ሲፒኦ ብቻ በማሰራት ከዋናው የዋጋ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

3.     ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ዘወትር በስራ ሠዓት እስከ ቀኑ አስር ሠዓት ድረስ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመከፈል ደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ከኢንተርፕራይዙ ቢሮ መውሰድ ይችላሉ፡፡

4.     ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሣባቸውን የያዘ የዋጋ ሰነድ ዋናና ቅጅ ለየብቻው በታሸገ ኢንቨሎኘ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ቀናት እስከ 15ኛው ቀን ከጠዋቱ 400 ሰዓት ድረስ ብቻ በኢንተርፕራይዙ ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡

5.     ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው እንዲሁም ጨረታውን መታዘብ የሚፈልግ ማንኛውም አካል በተገኙበት ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ በወጣ 15ኛው ቀን ከጠዋቱ 400 ታሽጎ 430 በግልፅ ይከፈታል፡፡ የመፈቻው ቀን በሳምንቱ የዕረፍት ቀናት ወይም በዓል ላይ ከዋለ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከላይ በተገለፀው ሰዓትና ቦታ በግልፅ ይከፈታል፡፡ ክክለኛው የመፈቻ ቀን በጨረታ ሰነዱ ላይ የሚገለፅ ይሆናል/

6.     ተጫራቾች በሌላ ተጫራች ዋጋ ላይ ተመስርተው የመወዳደሪያ ዋጋ ማቅረብ አይችሉም፡፡

7.     ኢንተርፕራይዙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

 

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥራችን /+251925750633/ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ

 

በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ መገዘዝ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ

Save Tender