Tender Detail

Tender Details


  የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን በበጀት አመቱ የሚያሰራጨውን የተለያዩ ዓይነት የደንብ አልባሳት ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡


                የጨረታ ማስታወቂያ

(ጨረታ ቁጥር ኢአጽ/ግንአዳ/RE/021/2018)

   የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን በበጀት አመቱ የሚያሰራጨውን የተለያዩ ዓይነት የደንብ አልባሳት ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

ተ.ቁ           የደንብ ልብሱ ዓይነት መለኪያ       ብዛት
1 ውስጥ ልብስ ብትን ጨርቅ ሜትር      1,440
2 ሻሽ ቁጥር  320
3 የተለያየ መጠን ያለው የወንዶች ሸሚዝ ቀለም ሰማያዊ ፣ ጥቁር ሰማያዊ እና ነጭ ቁጥር 2,144
4 ጉርድ ቆዳ ጫማ የወንድ ከ36 ቁጥር ጀምሮ ጥንድ 1,072
5 ጉርድ ቆዳ ጫማ የሴት ከ35 ቁጥር ጀምሮ ጥንድ  320
6 ክራቫት ጥቁር ሰማያዊ ቀለም ቁጥር 1,600
7 ካልሲ የተለያየ ቀለም ጥንድ 4,400
8 የደህንነት መከላከያ ጫማ (ሴፍቲ ጫማ) ጥንድ   500
9 የድርጅቱ ዓርማ (Logo) ያለው በአንደኛ ደረጃ ቴትረን 6000 ጨርቅ የተሰፋ ሜንዞ ቱታ (ኮትና ሱሪ ያለው)

ቀለም፡ ጥቁር ሰማያዊ

ሳይዝ (ልኬት)፡ ሰራተኞችን በመለካት በሚገኝ ልኬት መሰረት የሚሰፋ

ቁጥር 150
10

 

ጆሮ የሚሸፍን ኮፍያ ቀለም ጥቁር ሰማያዊ የድርጅቱ ዓርማ የሚታተምበት ቁጥር 200
11 ባርኔጣ (የጥበቃ ኮፍያ) ቀለም ጥቁር ሰማያዊ የድርጅቱ ዓርማ የሚታተምበት ቁጥር 700
12 የአፍና አፍንጫ መከላከያ ማስክ (Mask) ቁጥር 150
13 ከቆዳ የተሰራ የእጅ ጓንት ጥንድ 600
14 የድርጅቱ ዓርማ (Logo) ያለው ጋዋን

በአንደኛ ደረጃ ቴትረን 6000 ጨርቅ የተሰፋ

ቀለም፡ ጥቁር ሰማያዊ እና ነጭ

ቁጥር 1,000
15 ቲ-ሸርት ቁጥር 400
15 ፕላስቲክ ቦትስ ጫማ ቁጥር 300
16 ካፖርት ቁጥር 300

ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለጹትን መስፈርቶች የሚያሟሉ አቅራቢዎች በጨረታው እንዲሳተፉ ተጋብዘዋል፡፡

  • በጨረታው የሚወዳደሩ ተጫራቾች ሕጋዊ የታደሰ የንግድ ሥራ ፍቃድ ያላቸውና በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ ለመመዝገባቸው ከድረገጹ (website) አትመው ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  • ተጫራቾች በተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ከፋይነት የተመዘገቡ ፣ የግብር መለያ ሰርተፊኬት ያላቸው መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት እና የታክስ ክሊራንስ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  • ድርጅቱ ለሚገዛቸው ማንኛውም አይነት ጫማዎች የሚወዳደሩት አምራቾች ብቻ ይሆናሉ፡፡
  • ተጫራቾች በከፊል ወይም በሙሉ መጫረት ይችላሉ::
  • ተጫራቾች ከሚጫረቱት አልባሳት ውስጥ ከአንድ እስከ አራት ዓይነት የደንብ ልብስ ለመጫረት የጨረታ ማስከበሪያ ብር 150,000.00 (አንድ መቶ ሃምሳ ሺ) እንዲሁም ከአራት ዓይነት በላይ የደንብ አልባሳት ለመጫረት የሚፈልጉ ብር 250,000.00 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺ) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (cpo) ወይም ለዘጠና ቀናት የሚቆይ ቅድመ ሁኔታ ያላስቀመጠ የባንክ ዋስትና ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው::
  • ተጫራቾች የማይመለስ ብር00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለገሐር በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 108 ድረስ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
  • ተጫራቾች መወዳደሪያ ሠነዳቸውን በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ለገሐር በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 108 በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም. እስከ 8፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኢንተርፕራይዝ አገልግሎት ጽ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ በዚሁ እለት ማለትም ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 8:30 ይከፈታል፡፡
  • መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
  • ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 011-5512400 የውስጥ መስመር 237/262 ወይም በቀጥታ 011-5504931 መጠየቅ ይቻላል፡፡

የኢትዮጵያ መድን ድርጅት

Save Tender