በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 13 አስተዳደር እና ፋይናንስ ጽ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት የነኛ ዙር ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋልጋል፡፡
የግስጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 13 አስተዳደር እና ፋይናንስ ጽ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት የነኛ ዙር ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋልጋል፡፡ በመሆኑነ "ሆኑም ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች እንድትወዳደሩ እያሳወቅን፡፡
|
ተ.ቁ |
የእታው አይነት |
የሎት አይነት |
የጨረታ ማስከበሪያ ብር መጠን |
|
1 |
ስቴሽነሪ እና ተነሮች መሳሪያዎች |
ሎት 1 |
30,206.96 ብር |
|
2 |
የፅዳት ፅቃ |
ሎት 2 |
59,825.088 ብር |
|
3 |
የደንብ ልብስ |
ሎት 3 |
36,521,56 ብር |
|
4 |
ልዩ ልዩ የቢሮ መገልገያ ዕቃዎች |
ሎት 4 |
6000 -ብር |
|
5 |
ፈርኒቸር ፅቃዎች |
ሎት 5 |
20,000 ብር |
|
6 |
የመስተንግዶ አቅርቦት |
ሎት 6 |
8,000-ብር |
|
7 |
የትራንስፖርት አገልግሎት |
ሎት 7 |
15,000 ብር |
|
8 |
የህትመት አገልግሎት |
ሎት 8 |
13,000 ብር |
|
9 |
የኤሌክትሮኒክስ ጥገና አገልግሎት |
ሎት 9 |
4,000 ብር |
|
10 |
የመድረክ ኢቃዎችኪራይ አገልግሎት |
ሎት 10 |
5,000-ብር |
1. በጨረታ ለመወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች በዘመኑ ህጋዊ የሆነ የታደሰ የንግድ ፍቃድ፣ ቲን ነምበርያለው እና የቫት ተመዝጋቢ መሆን አለበት፡፡
2. በጨረታው የሚወዳደሩ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ብቻ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
3. ተጫራቶች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችል በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ ለመሆኑ ማስረጃ ከሰነዱ ጋር ማቅረብ የሚችል፡፡
4. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት እቃ ናሙና ማቅረብ አለባቸው፡፡
5. ተጫራቾች ዋጋ ሲሞሉ ስርዝ ድልዝ ቢፈጠር ከፊት ለፊቱ ፊርማ ሊኖረው ይገባል፡፡ አለበለዚያ የተሞላው ዋጋ ተቀባይነት የለውም፡፡
6. የጨረታ ሰነዱ አንዱ የጨረታ መመሪያ መሆኑን ተጫራቾች ሊረዱት የሚገባ ሲሆን በጨረታ ሰነዱ ላይ ያልተካተቱ ችግሮች ቢያጋጥሙን በግዥ መመሪያው መሰረት የሚዳኝ ይሆናል፡፡
7. ጨረታውን ለማወዳደር የእቃ ጥራት የዋጋ ዝቅተኝነት ወ.ዘ.ተ ግምት ውስጥ የምናስገባ ይሆናል፡፡
8. ጨረታውን ለማዛባት ወይም እንቅፋት ለመፍጠር የሚሞከሩ ተጫራቾች ከጨረታ ውጪ የሚሆኑ ሲሆን ወደፊትም በመንግስት ግዥ መመሪያ መሰረት በህግ እንዲከሰሱ ይደረጋል፡፡
9. ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ዋጋ ለውጥ ማሻሻያ ማድረግና ራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡ እንዲሁም ከስፔስፊኬሽን ወይም ካቀረቡት ናሙና ውጭማቅረብ አይችሉም፡፡
10. ጨረታው በሁለት ኢንቨሎፕ የሚቀርብ ሆኖ ኦርጂናል እና ኮፒ የጨረታ ሰነድ የሚል ጽሁፍ እንዲሁም ሙሉ የጨረታ ሰነዱ ኮፒ ተደርጎ በአቅራቢው ድርጅት ማህተም ተረጋግጦ ተመላሽ መሆን ይገባል፡፡
11. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይየስራ ቀናት ከፍት ሆኖ የሚቆይ ይሆናል፡፡
12. ተጫራቾች መጫረቻ ስነዶችን ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ እስከ 10ኛው ቀን ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በ1ዐኛው ቀን 11፡00 የሚታሸግ ሲሆን ቀጣዩ ቀን የስራ ቀን ከሆነ ጠዋት 3፡30 ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም የሚከፈትና የሚለይ ይሆናል፡፡
13. የመወዳደሪያ ሰነዱን ቦ/ክ/ከ/ወ/13/ አስተዳድር እና ፋይናንስ 4ኛ ፎቅ በመቅረብ አንድ ሎት ዋጋ የማይመለስ 200 (ሁለት መቶ) ብር በመከፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
14. አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ በማስያዝ ውል መያዝ አለባቸው፡፡ በተጨማሪም ውሉን ከተዋዋሉ በኃላ እቃውን በ10 ቀናት ውስጥ በአስተዳድሩ ግቢ ውስጥ ባለው ንብረት ከፍል አጠናቀው ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጽ/ቤቱ 20% መጨመር ወይም 20% መቀነስ መብቱ የተጠበቀነ ነው፡፡
15. ማሳሰቢያ - የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ፡- ገርጂ ታክሲ ተራ ወረዳ 13 አስተዳድርና ፋይናንስ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር41 በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር፡- 0118931655 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 13 አስተዳደርእና ፋይናንስ ጽ/ቤት
