በኦሮሚያ ከልል በሰሜን ሸዋ ዞን የደ/ሊባኖስ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2019 የበጀት ዓመት ለወረዳው እና ለESRP ፕሮጄክት አገልግሎት የሚውል የሰራተኞች የደንብ ልብስ፣ አላቂ የጽህፈት መሳሪያዎች፣ የጽዳት እቃዎች፣ ኤሌክትሮኒከስ እቃዎች የመኪና ጎማዎች የቤት ቆርቆሮ እና ሚስማር ሲሚንቶ ፈርኒቸሮችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ገልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በኦሮሚያ ከልል በሰሜን ሸዋ ዞን የደ/ሊባኖስ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2019 የበጀት ዓመት ለወረዳው እና ለESRP ፕሮጄክት አገልግሎት የሚውል የሰራተኞች የደንብ ልብስ፣ አላቂ የጽህፈት መሳሪያዎች፣ የጽዳት እቃዎች፣ ኤሌክትሮኒከስ እቃዎች የመኪና ጎማዎች የቤት ቆርቆሮ እና ሚስማር ሲሚንቶ ፈርኒቸሮችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በጨረታው ስመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-
የቫት ተመዝጋቢ የሆነ፣ የዘመኑን የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያለው፣ የዘመኑን የመንግስት ግብርየከፈለ፣ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር ባወጣው የእቃ አቅራቢዎች ዝርዝርየተመዘገቡበትን ማስረጃ የሚያቀርቡ እና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ መሆን አለባቸው፡፡ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 የስራ ቀናት የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ብር 500 አምስት መቶ ብር/ በመከፈል ደብረ ሊባኖስ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 1 መግዛት ይችላሉ፡፡ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000/አስር ሺህ ብር/ በባንከ በተመሰከረለት ቼከ/CPO/ብቻ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራቾች እቃዎቹን ከነ ትራንስፖርት ወጭያቸው የሚሸጡብትን ዋጋና አይነት በመለየት በተዘጋጀው ዝርዝር ሰነድ ላይ ሞልተው በታሸገ ኢንቨሎፕ ኦርጅናል እና ኮፒ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን አንስቶ እስከ 15ቀን ዘወትር በስራ ሰዓት 2፡30-11፡30 ድረስ በስራ ቀናት ውስጥ ለዚህ ሲባል በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በ16ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ተዘግቶ በዚህ ቀን በ5፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡ 16ኛው ቀን ቅዳሜ እሁድ ወይም በበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይካሄዳል፡፡
ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች ባሸነፈባቸው የእቃ ዝርዝር መሰረት ከመ/ቤቱ ጋር የውል ስምምነት መፈራረም ይኖርበታል፡፡
ተጫራቾች በሚፈልጉትና ማቅረብ በሚችሉበት እቃዎች ላይ ብቻ መወዳደር ይችላሉ፡፡ ሆኖም ለአንድ ዓይነት እቃ ከተጠየቀው ብዛት አሳንሶ ማቅረብ አይቻልም፡፡
ተጫራቾች በጨረታው ተወዳድረው ያሸነፉበትን እቃዎች ደ ሊባኖስ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት እቃ ግምጃ ቤት የማጓጓዣ የማስጫኛና የማውረጃ ወጪ መቻል ይኖርባቸዋል፡፡
መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ተጫራቾች የሚጫረቱበትን የእቃ አይነት ወይም ናሙና ማቅረብ አለባቸው፡፡
ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0963226105 ዘወትር በስራ ሰዓት በመደወል ወይም ደ/ሊባኖስ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት እቃ ግዥ ከፍል በግንባር ቀርበው መረዳት ይችላሉ፡፡
አድራሻ፡- ሰሜን ሸዋ ዞን የደ/ሊባኖስ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት ከአ/አ በስተ ሰሚን 89 ኪ.ሜ ላይ ይገኛል።
ሸረሮ ከተማ
በሰሜን ሸዋ ዞን የደ/ሊባኖስ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
