በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በኢሉባቦር ዞን ያዮ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት በወረዳው ለሚገኙ መሥሪያ ቤቶች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን የተለያዩ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በኢሉባቦር ዞን ያዮ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት በወረዳው ለሚገኙ መሥሪያ ቤቶች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን የተለያዩ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
- የፅህፈት መሣሪያ
- የሞተር ሳይክል
- የሠራተኛ ደንብ ልብስ
- የተለያዩ ጎማዎች ከእነ ከለመዳሪ
- የቢሮ ቋሚ ዕቃዎች / Furniture/
- የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች
ከዚህ በታች የተዘረዘረውን መስፈርት የምታሟሉ ተጫራቾች ወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
1. በስራው ዘርፍ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ እና የ2018 ግብር ከፍሎ ፍቃዱን አሳድሶ ያጠናቀቀ።
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያለው፣ የቫት ወይም ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆነ
3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚመለስ 50,000 (ሃምሳ ሺህ) ብር በሲፒኦ (cpo )ለእያንዳንዱ ዶክመንት ማስያዝ የሚችል
4. የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ ሰነድ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ባሉት 15 (አስራ አምስት) የሥራ ቀናት የማይመለስ 500 (አምስት መቶ) ብር በመክፈል ከያዮ ወረዳ ገ/ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት መውስድ ይችላሉ።
5. የሚወዳደሩበት ሰነድ ስርዝ ድልዝ የሌለው እና የሚነበብ መሆን አለበት ስርዝ ድልዝ ካለው ውድቅ ይሆናል። ተወዳዳሪዎች ዋጋን የሚገልፅ ሰነድ ኦርጂናል እና ኮፒዉን ለየብቻ ፍቃድ እና የተለያዩ ተፈላጊ ሰነዶችን አያይዞ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
6. የጨረታ አሸናፊ የሆኑ ድርጅቶች ሆነዉ የተመረጡ የጨረታዉ ዉጤት በደብዳቤ ከተገለፀላቸዉ ቀን ጀምሮ በአስር ቀናት ዉስጥ በመቅረብ ያሸነፉበትን ዋጋ 10% ለመልካም ሥራ አፈፃፀም ዋስትና በማስያዝ ዉል መፈረም አለባቸው።
7. ጨረታዉ ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ 60 (ስልሳ )ቀናት ይሆናል።
8. ተጫራቾች የዕቃ ዝርዝር ጨረታ መወዳደሪያ በሚያቀረቡት ዋጋ ላይ ቫት ጨምሮ ወይም ያለቫት በማለትበመጨረሻዉ ገጽ ላይ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል። መስሪያ ቤቱ የዕቃዉን ብዛት 20% ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል።
9. የሰራተኛ ደንብ ልብስ ለማቅረብ የሚወደደሩ ተወዳዳሪዎች የእቃዉን ናሙና ከጨረታዉ ስነድ ጋር ማቅረብ አለባቸው።
10. ፈርኒቸር ዕቃዎች ላይ የምትወዳደሩ ድርጅቶቸ እስከ መግጠም ድረስ ይሆናል።
11. በራሱ ወጪ ወይም ትራንስፖርት እስከ ያዮ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት አቅርቦ ማስረከብ አለበት።
12. ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ስነድ ዘወትር በሥራ ሰዓት ዋጋ በመሙላት ለጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን በያዮ ወረዳ ገንዘብ ት/ጽ/ቤት እስከ በ15ኛው ቀን እስከ 11፡30 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
13. ጨረታዉ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 የስራ ቀናት ቆይቶ በ16ኛ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተጠናቅቆ በዚያው ቀን 4፡30 ሰዓት ላይ ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ይከፈታል።
14. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ በ4፡30 ሰዓት ለይ ይከፈታል። ጨረታው በሚከፈትበት ዕለት በዓል ከሆነ ወደ ሚቀጥለው የሥራ ቀን ተላልፎ ጨረታው ይከፈታል።
15. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 047 333 0352
በኢሉባቦር ዞን የያዮ ወረዳ ገንዘብ/ጽ/ቤት
