Tender Detail

Tender Details

  • Company በሸገር ከተማ ሱሉልታ ክ/ከተማ የወሰርቢ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
  • Address ሱሉልታ ፡ ኦሮሚያ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0910821521
  • Website
  • Deadline11 Sep 2026, 9:00 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Price500 ብር ብቻ ነው
  • opening dateበዚያውኑ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት
  • Categories Cleaning & Janitorial , Electrical And Electromechanical , Office Supplies And Services

በሸገር ከተማ ሱሉልታ ከ/ከተማ የወሰርቢ ወረዳ ገንዘብ ፅ/ቤት ለሚገኙ ሴክተሮች የጽህፈት መሣሪያዎች፡- አላቂ ፣የጽዳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ፈርኒቸር መመሪያ Bidders instruction


የጨረታ ማስታወቂያ

በሸገር ከተማ ሱሉልታ ከ/ከተማ የወሰርቢ ወረዳ ገንዘብ ፅ/ቤት ለሚገኙ ሴክተሮች የጽህፈት መሣሪያዎች፡- አላቂ ፣የጽዳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ፈርኒቸር መመሪያ Bidders instruction

ሀ. የተወዳዳሪዎች መመሪያ

  1. ተጫራቾች በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ሆኖ ሀ. የዘመኑን ግብር በመከፈል የ2019 የታደሰ ንግድ ፍቃድ ማስረጃ ለ. የገ/ኢ/ልማት ሚንስቴር የዕቃ ዓቅራቢነት የምዝገባ ማስረጃ ሐ. የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ መወዳደር ይችላሉ ።
  2. ተጫራቾች ከማንኛውም የሙስናና የብክነት ድርጊቶች ነጻ የሆኑና በፌዴራልና በከልል የወጡትን የግገዢ ደንቦች በማከበር ሰነዱ ውስጥ የቀረቡትን ግዴታዎች አምነውበት መፈፀም ይኖርባቸዋል።
  3. ማንኛውም ተጫራች ጨረታውን በህገወጥ መንገድ ሊያራምድ የሞከረ ከጨረታው ወጪ ከመሆኑም በላይ ለወደፊቱ በሚካሄዱ ጨረታዎችን ላይ እንዳይሳተፉ ተደርጎ ያስያዘው የጨረታ ማስከበሪያ ይወረስበታል።
  4. ተጫራቾች ወደ ጨረታው ለመቅረብ ግዴታዎቻቸውን የተወጡና የተጠየቀውን ስፔስፍኬሽን በማሟላት የወቅቱን ገበያ ያገናዘበ ዋጋ ያቀረበ መሆን አለባቸው።
  5. ተጫራቾች መ/ቤቱ ባቀረበው እቃ ዝርዝር በሙሉ ወይም በሚፈልገውም የእታ ዝርዘር ላይ መጫረት ይችላል እንጂ ተጫራቹ የተወሰነ እቃ ለይቶ ማቅረብ አይችልም።
  6. የተወዳሪዎች ሃሳብ ሰነድ ሲቀርብ የእቃው አስፔስፊኬሽን፣ የእቃው አይነት፣የተመረተበት ሀገር ስም፤ የእቃው መለያ ሞዴል ቁጥር የተመረተበት ዓመተ ምህረት /ስፔስፍኬሽን ላይ መግለጽ አለበት።
  7. አሸናፊ ተጫራቾች የቅድመ ከፍያ ከጨረታው እቃ 50% ገቢ ካደረጉ በኋላ ከጠቅላላው ዋጋ 30% ብቻ መጠየቅ ይችላሉ።
  8. አንድ ተጫራች በሰጠው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት አይቻልም።
  9. ማንኛውም ተጫራች የሚወዳደርበትን የእቃ አይነት የነጠላ ዋጋ ማቅረብ ይኖርበታል።
  10. የሚቀርበው ዋጋ የወቅቱን አካባቢ ገበያ ያገናዘበ መሆን ይገባዋል።
  11. የእቃው ሞዴል ወይም ስዕል ናሙና ከጫረታ ሰነዱ ጋር ይቀርባል።
  12. መስሪያ ቤቱ ባቀረበው ጨረታ ላይ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብት አለው።
  13. አሸናፊ ተጫራች ተወዳዳሪ/ የውድድሩ ውጤት ከተነገረበት 5-10 ቀን ቀርቦ ውል ካልፈጸመ ከጨረታ መሰከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ይወረሳል።
  14. የጨረታው የመወዳደሪያ ሃሳብ ሰነድ ኦርጅናልና አንድ ፎቶ ኮፒ በተለያዩ አንድ ፖስታዎች ከተፈላጊ መረጃዎች ጋር ተያይዞ በሰም ታሸገ ኢንቨሎፕ ይቀርባል።
  15. የሚቀርበው ሰነድ ሙሉ አድራሻ የተጻፈበት ሆኖ በሚመለከተው ባለስልጣን የተፈረመበትና በማህተም የተረጋገጠ መሆን አለበት፡፡
  16. ጨረታው በሸገር ከተማ ሱሉልታ ከ/ከተማ የወሰርቢ ወረዳ ገንዘብ ፅ/ ቤት አንድ/1/ከ-230 እስከ 12፡30 ሰዓት ድረስ መግዛት ይቻላል።
  17. ተጫራቾች የጨረታውን መወዳደሪያ ሀሳብ ሰነድ የያዘ ፖስታ ጫረታውን ከገዙበት ቀን ጀምሮ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  18. ጨረታው በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያውኑ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾቹ ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
  19. ተጫራቹ ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሰዓቱ ባይገኙም የጨረታው ሳጥኑ ይከፈታል።
  20. ሰነዱን ለመመርመርና ለመገምግም የሚጠቅም ሆኖ ከተገኘ መስሪያ ቤቱ ተጫራቾቹ ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሀሳብ ሰነድ ላይ መግለጫ መጠየቅ ይቻላል።
  21. ጨረታውን በመመርመር ሂደት ላይ የተገኘውን የሀሳብ ስህተት ማስተካከል ይቻላል። ድርጊቱ ወዲያው የመወዳደሪያ ሀሳብ ሰነድ ላቀረበው ከፍል ይገለጽለታል።
  22. ጨረታው ከተከፈተ በኋላ የቀረበውን የውድድር ሀሳብ መቀየር ማሻሻል ወይም ከጨረታው ውስጥ ራስን ማግለል አይቻልም።
  23. አሸናፊ ተጫራቶች የውል ማስከበሪያ የጨረታ ውጤት ከተነገረበት 5-10 ቀን ውስጥ ከግዢው ዋጋ ላይ 10% በባንክ በተመሰከረ ቼክ ወይም /CPO/ በማቅረብ የግዢው ውል መፈረም ይኖርበተል።
  24. የጨረታው ማስከበሪያ አሸናፊው ከታወቀ ለተሸናፊው ይመለስለታል።
  25. ለእሸናፊ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የውል ማስከበሪያውን ገቢ አድርጎ ከጨርስ በኃላ ይመለስለታል።
  26. አሸናፊው ተጫራች ውል ከፈጸመ በኋላ በዐ ቀን ውስጥ እቃውን አጠናቆ ማቅረብ አለበት።
  27. የጨረታው ዋጋ የጨረታውን ውጤት ከተነገረበት ቀን እንስቶ ዕቃውን ማስረከቢያ ቀን ድረስ ያለምንም ለውጥ መቆየት አለበት።
  28. ተወዳዳሪዎች ጨረታውን ካሸነፈ እቃዎቹን በሙሉ በራሳቸው ትራንስፖርት ማውጫና ማውረጃ ችሎ የወሰርቢ ወረዳ ገንዘብ ፅ/ ቤት እቃ ግምጃ ቤት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  29. የሚቀርቡት ዕቃዎች የተቀደዱ፣ የተሰበሩ፥ የተበላሹና ከአገልግሎት ውጪ ከሆነ መሥሪያ ቤቱ አይቀበላቸውም።
  30. መ/ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊልም የመሰረዝ መብት የተጠበቀ ነው:: የሰነድ መሸጫ የማይመለስ 500 ብር ብቻ ነው።
  31. ተጫራቶች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 100,000 / መቶ ሺህ ብር /በባንክ በተመሰከረለት (ቼከ/ብቻ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
  32. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0910821521 በዚህ ስልከ ቁጥር ደውለው ሚፈልጉትን መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

በሸገር ከተማ ሱሉልታ ክ/ከተማ የወሰርቢ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

✨ messages.ai_summary
Tender for office supplies, cleaning materials, electronics, and furniture for sectors under the Wersebi District Finance Office, Sululta Sub-City. Bidders need valid trade licenses, tax clearance, supplier registration, and VAT registration. Bids must cover full item lists; delivery to the office warehouse is required.
Save Tender