የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 አጠገብ የሚገኘው የቡልቡላ ራዕይ የመጀ/ደ/ት/ቤት ለት/ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ፡-
የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
የግዥ መለያ ቁጥር 001/2019
የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 አጠገብ የሚገኘው የቡልቡላ ራዕይ የመጀ/ደ/ት/ቤት ለት/ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ፡-
|
ተ.ቁ
|
የሎት አይነት
|
የማስያዣ ዋጋ
|
|
1
|
ሎት 1 የደንብ ልብስ
|
12,000
|
|
2
|
ሎት 2 አላቂ የቢሮ እቃዎች
|
10,000
|
|
3
|
ሎት 3 የህትመት ስራ
|
4,500
|
|
4
|
ሎት 4 አላቂ የህክምና እቃዎች
|
500
|
|
5
|
ሎት 5 አላቂ የትምህርት እቃዎች
|
15,000
|
|
6
|
ሎት 6 የፅዳት እቃዎች
|
10,000
|
|
7
|
ሎት 7 ልዩ ልዩ መሳሪያዎች
|
3,000
|
|
8
|
ሎት 8 ፕላንትና ማሽነሪ እቃዎች
|
15,000
|
|
9
|
ሎት 9 ቋሚ እቃዎች
|
16,000
|
|
10
|
ሎት 10 የጭነትና ትራንስፖርት አገልግሎት
|
4,000
|
ቋሚ እቃ፣ የትምህርት መሳሪያዎች፣ ህትመትና፣ የኤሌክትሪክ እቃዎች፣ የህክምና እቃ፣ የፅዳት እቃዎችን፣ የተለያዩ የኤሌክትሪክ እቃዎች ለማስጠገን ይፈልጋል።
ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን። ስለሆነም፡-
1. በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድና ቲን ነምበር /TIN NO/ ያላችሁ።
2. የዘመኑ ግብር የከፈሉና በአቅራቢዎች ዝርዝር ላይ የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚገልፅ መረጃ የሚያቀርብ።
3. በተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ለመሆናቸው የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል።
4. አሸናፊ ተጫራቾች የውል ማስከበሪያ 10% ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
5. የጨረታ ማስከበሪያ የሎቱ ከባንክ በተረጋገጠ ቼክ /C.P.O/ ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዞ ማቅረብ የሚችል።
6. የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከት/ቤቱ ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 05 በመቅረብ መግዛት ይቻላል።
7. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 /አስር/ ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የጨረታ ሰነዱን በተዘጋጀው ኦርጅናልና ኮፒውን በፖስታ በማሸግ ት/ቤቱ የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
8. ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው ቀን በስራ ቀናት ውስጥ 4:00 ሰዓት ሲሆን ጨረታው የሚከፈተው በዚሁ ዕለት 4:30 ሰዓት ይሆናል።
9. የጨረታው አሸናፊ የአሸነፈውን እቃ በሚደረገው የውል ስምምነት መሰረት በራሱ ትራንስፖርት በወረዳ 12 አጠገብ በሚገኘው የቡልቡላ ራዕይ የመጀ/ደ/ት/ቤት ንብረት ክፍል ድረስ ማቅረብ ይኖርበታል።
10. ተጫራቾች ለሚያቀርቧቸው እቃዎች ጨረታ ከመከፈቱ በፊት ከእያንዳንዱ አላቂና ቋሚ እቃዎችን በመለየት ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ከባድ ከሆኑ ግን በፎቶ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
11. ጨረታው የሚከፈተው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይሆናል።
12. መስሪያ ቤቱ ውል ከወሰዳቸው እቃ ላይ 20% የመጨመር እና የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ይሆናል። መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 አጠገብ
መረጃ ፡- 011 822 9969
በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 የቡልቡላ ራዕይ የመጀ/ደ/ት/ቤት
