የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ለ2019 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውልና ቀጥሎ የተዘረዘሩትን፤
የጽህፈት መሣሪያዎች፣ የፕሪንተር ቀስሞች እና የንጽህና/የጽዳት ዕቃዎች ግዥ
የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር፣ ኦ.ደ.ዱ.እ.ድ- 02/2019
የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ለ2019 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውልና ቀጥሎ የተዘረዘሩትን፤
- ሎት 1፡ የጽህፈት መሣሪያዎች
- ሎት 2፡ የፕሪንተር ቀስሞች
- ሎት 3፡ የንጽህና/የጽዳት ዕቃዎች
በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ደፍሏል፡፡
በዚሁ መሠረት ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉና በዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶች ወይም ግለሰቦች በጨረታው ላይ በሙሉም ሆነ በከፊል እንዲሳተፉ መ/ቤቱ ይጋብዛል፡፡
- በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ምዝገባ የምስክር ወረቀት ያላቸውና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ እንዲሁም የዘመኑን ግብር ከፍለው በጨረታ ላይ ለመሳተፍ ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ በጨረታ ላይ መሳተፍ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 1000.00 (አንድ ሺህ) ብር በመከፈል፣ አዲስ አበባ ከተማ ቀበና አይል ሊቢያ ከፍ ብሎ ከሚገኘው የድርጅቱ ዋና መ/ቤት፣ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 401 በመቅረብ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ውስጥ ተያይዞ በቀረበው የዋጋ ማቅረቢያ ፎርም ላይ የተዘረዘሩትን ዕቃዎች በማየት እያንዳንዱን ዕቃ የሚያቀርብበትን ዋጋ በመሙላት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 50,000.00 (ሀምሳ ሺህ) ከታወቀ ባንክ በኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ስም ሲፒኦ (CPO) ወይም የባንክ ዋስትና (Bank Gurantee) በማሠራት ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር አብሮ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሠነዳቸውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብና ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት የሚጠበቅባቸው ሲሆን፤ ጨረታው መስከረም 05 ቀን 2019 ዓ.ም ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዚያው ቀን ከጠዋቱ 4:30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከታች በተገለጸው አድራሻ ይከፈታል።
- ተጫራቾች ጨረታው በሚከፈትበት ዕለት ናሙና ለተጠየቀላቸው ዕቃዎች ናሙና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች አንዱ ተጫራች ባቀረበው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይችልም፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለተጨማሪ መረጃ - ከታች የተገለጸውን ስልክ ቁጥር በመደወል ወይም በፋክስ፣ በጽሑፍ መጠየቅና ማብራሪያ ማግኘት ይችላሉ፡፡
አድራሻ፡-
የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 07
ስልክ ቁጥር፡- 011-122-00-20/011-124-02-58
የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት
✨ messages.ai_summary
Oromia Forest and Wildlife Enterprise invites bids for office supplies, printer cartridges, and cleaning materials across three lots. Eligible bidders must hold a renewed trade license, tax clearance, and VAT registration. Bids may cover all or part of the lots.
