በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በጅማ ዞን የጉማይ ወረዳ ገንዘብ /ጽ/ቤት በወረዳው ለሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች በ 2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት የመኪና ጥገና፣ መለዋወጫዎችን፣ ፈርኒቸር፣ ምግብ፣ ለጭነት የተወሰደ የሚያገለግሉ መኪኖች እንዲሁም ጎማ እና የደንብ ልብስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 831-01
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በጅማ ዞን የጉማይ ወረዳ ገንዘብ /ጽ/ቤት በወረዳው ለሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች በ 2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት የመኪና ጥገና፣ መለዋወጫዎችን፣ ፈርኒቸር፣ ምግብ፣ ለጭነት የተወሰደ የሚያገለግሉ መኪኖች እንዲሁም ጎማ እና የደንብ ልብስ በግልጽ ጨረታ ከዚህ በታች በተዘረዘረው መስፈርት መሰረት ተጫራቾች ማሟላት የሚጠበቅባቸው መስፈርቶች፡-
- የ2017 ዓ.ም ግብር የከፈሉ፤
- 2.በዘርፉ የ2018 ዓ.ም የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸዉ፤ የግብር መክፈያ ወቅት ካለቀ መወዳደር ይችላሉ
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያለው፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ የሆኑ እና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል
- የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት ያላቸው
- ለጨረታ ሰነድ የጨረታ ማስከበሪያ ዋጋ ብር 10,000.00 /አስር ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ (CPO) ማስያዝ የሚችል፤
- የጨረታውን ዝርዝር ሰነድ የማይመለስ ብር 400 /አራት መቶ/ በመክፈል ከገንዝብ/ጽ/ቤት መግዛት የሚችል
- ተወዳዳሪዎች ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 የስራ ቀናት የጨረታ ሰነዱን ገዝቶ ማስገባት የሚችል
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በጨረታ ሰነዱ ላይ በመሙላት ኦርጅናል እና ኮፒውን በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ ሙሉ አድራሻውን እና የድርጅቱን ስም እና ማህተም በማድረግ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአስራ ስድስተኛው (16) ቀን 6:00 ሰዓት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፤
- ጨረታዉ በተባለበት ቀን እና ሰዓት ገብቶ ካለቀ በኋላ በእለቱ 6:30 (ስድስት ሰዓት ተኩል) ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ8:00 (ስምንት ሰዓት) በጉ/ወ/ገ/ጽ/ቤት ይከፈታል፣
- አሸናፊ ተጫራቾች ከጽህፈት ቤቱ ጋር ውል መፈራረም የሚችሉ እና የውል ማስከበሪያ /ዋስትና/ ያሸነፈበትን ዋጋ 10% በቼክ ማስያዝ የሚችሉ መሆን አለባችው፡፡
- ከዚህ ማስታወቂያ ላይ ያልተጠቀሱ መስፈርቶችን ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ።
ማሳሰቢያ፡- ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ / በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር +251967671200 ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
በጅማ ዞን የጉማይ ወረዳ ገንዘብ/ጽ/ቤት
