የሄጦሳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 የበጀት ዓመት በወረዳው ለሚገኙ ጽ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ቋሚ የቢሮ አሌክትሮኒክስ፣ ፈርኒቸር፣ የጽህፈት መሣሪያዎች፤ የጽዳት ዕቃዎች፣ የሠራተኞች የደንብ ልብስ፣ እና የመኪና ጎማዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁ-01/2018
የሄጦሳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 የበጀት ዓመት በወረዳው ለሚገኙ ጽ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ቋሚ የቢሮ አሌክትሮኒክስ፣ ፈርኒቸር፣ የጽህፈት መሣሪያዎች፤ የጽዳት ዕቃዎች፣ የሠራተኞች የደንብ ልብስ፣ እና የመኪና ጎማዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም:-
- ለተጠየቁት የግዥ ዕቃዎች ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር ከፍለው የንግድ ፈቃዳቸውን ያሳደሱ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (Tax Payer Registration No.) ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ እና በፌዴራል፣ በክልል ወይም በዞን ገንዘብ ጽ/ቤት ወይም በግዢዎችና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት ያላቸው ዋናውንና ኮፒውን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች ለቋሚ የቢሮ ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ ለጽህፈት መሣሪያዎች እና ለመኪና ጎማዎች ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ) ፣ ለቋሚ የቢሮ ፈርኒቸር ዕቃዎች፤ ለጽዳት ዕቃዎች፣ እና ለደንብ ልብስ ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 150.00 (አንድ መቶ ሃምሳ ብር) በሄጦሳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ስም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሂሳብ ቁጥር 1000076363572 ገቢ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የሥራ ቀናት የጽ/ቤቱ የግዥ፣ ንብረት አስተዳደር፣ ማስወገድና ጠቅላላ አገ/ ቢሮ ቁጥር 6 ድረስ በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ከግብር ሰብሳቢው መ/ቤት የዘመኑን ግብር አጠናቀው ለመክፈላቸው እና በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን ደብዳቤ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ በመሙላት በዝግ ፖስታ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ እስከ 16ኛው የሥራ ቀናት ማቅረብ የሚኖርባቸው ሲሆን፤ ጨረታው በ16ኛው የሥራ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ዕለት ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በጽ/ቤቱ የስብሳባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- ማንኛውም ተጫራቾች ለቋሚ የቢሮ ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፤ ለጽህፈት መሣሪያዎች እና ለመኪና ጎማዎች ሰነድ የጨረታ ማስከበሪያ ለእያንዳንዱ ሰነድ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 20,000.00 (ሀያ ሺህ) ፤ ለደንብ ልብስ ሰነድ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 15,000.00 (አስራ አምስት ሺህ) እንዲሁም፣ ለጽዳት ዕቃዎች እና ለቋሚ የቢሮ ፈርኒቸር ዕቃዎች ለእያንዳንዱ ሰነድ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000.00 (አስር ሺህ) ፤ በአቅራቢያቸው በሚገኝ የታወቀ ባንክ በክፍያ ማዘዣ (C.P.O) ብቻ ማቅረብ አለባቸው።
- አሸናፊው ተጫራች ያለምንም የአቅርቦት ችግር አስተማማኝ የሆነ የዕቃ ክምችት ያለውና ዕቃዎቹን በራሱ የማጓጓዣ ወጪ ኢተየ ከተማ ውስጥ በሚገኘው የወረዳው ገንዘብ ጽ/ቤት ድረስ አምጥቶ ማስረከብ ይኖርበታል፡፡
- ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ ስ.ቁጥር 02233580012/0972990933/0911854342/ 0911903235 ይጠይቁ።
በአርሲ ዞን የሄጦሳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
