በቦሌ ከፍለ ከተማ የወረዳ 06 አስተዳደር ለ2018 ዓ.ም ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ እቃዎችን መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቁጥር 001/17
በቦሌ ከፍለ ከተማ የወረዳ 06 አስተዳደር ለ2018 ዓ.ም ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ እቃዎችን መግዛት ይፈልጋል፡፡
ሎት1. አላቂ የቢሮ እቃ/የጽሕፈት እቃዎች
ሎት 2. አላቂ የፅዳት እቃዎች
ሎት 3. ደንብ ልብስ
ሎት 4. ቋሚ እቃዎች
ሎት 5. የመኪና መለዋወጫ እቃዎች
ሎት 6. የህትመት ሥራዎች (ውጤቶች)
ሎት 7. የጭነት እና ትራንስፖርት አገልግሎት
ሎት 8. የጥገና አገልግሎት
ሎት 9. የመስተንግዶ አገልግሎት
ስለዚህ በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ድርጅቶች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ሕጋዊ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
- የመንግሥት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ባዘጋጀው የእቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ፡፡
- ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር አስገቢው ባለሥልጣን የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ለተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና / በየሎቱ 2% ማለትም
|
ሎት |
የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና cpo በብር |
|
ሎት.1 |
10,000 |
|
ሎት.2 |
15,000 |
|
ሎት.3 |
20,000 |
|
ሎት.4 |
15,000 |
|
ሎት.5 |
1,500 |
|
ሎት.6 |
10,000 |
|
ሎት.7 |
5000 |
|
ሎት.8 |
5000 |
|
ሎት.9 |
800 |
- ማንኛውም ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በየሎቱ በመግዛት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር ፋ/ጽ/ቤት 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 14 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን በታሸገ ኤንቨሎፕ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከ2:30 እስከ 11፡00 ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታው በ11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ በዛው ቀን 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተሰጠው ተመሳሳይ ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- የጨረታ አሸናፊ ከሆኑ ላሸነፉበት እቃ ዋስትና ወይም የውል ማስከበሪያ CPO 10% ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- በተጨማሪ መሥሪያ ቤቱ የጨረታውን 20% መቀነስ ወይም መጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች ለመጫረት ሲመጡ ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ናሙና የማይቀርብባቸው ቋሚ ዕቃዎች መሥሪያ ቤቱ ባቀረበው ስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ አለባቸው፡፡
- በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በመ/ቤቱ ግ/የሥራ ሂደት ክፍል ድረስ በአካል ወይም በስልከ ቁጥር 0118678129 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።
አድራሻ ፡- መገናኛ ወደ ጉርድ ሾላ በሚወስደው መንገድ ገባ ብሎ ውሃ እና ፍሳሽ ባለሥልጣን ዋና መሥሪያ ቤት ፊት ለፊት
ቦሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ 06 ፋይናንስ ጽ/ቤት
