በልደታ ክፍለ ከተማ ወ/6/አስተዳደር ፋ/ጽ/ቤት ለጽህፈት ቤቶች በ2018 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋቸውን ግብዓቶች ብቃት ያላቸውንና በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል።
አንደኛ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የግዥው መለያ ቁጥር - LS/C F/E/D 001/2018
በልደታ ክፍለ ከተማ ወ/6/አስተዳደር ፋ/ጽ/ቤት ለጽህፈት ቤቶች በ2018 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋቸውን ግብዓቶች፡-
ሎት 1 የትራንስፖርት አገልግሎት የጨረታ ማስከበሪያ ብር 14,000
ሎት 2 የጽሕፈት መሣሪያ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 32,677
ሎት 3 የደንብ ልብስ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 25,058
ሎት 4 የጽዳት እቃዎች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 49,610
ሎት 5 የቋሚ እቃ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000
ሎት 6 መስተንግዶ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 9,191
ሎት 7 ህትመት የጨረታ ማስከበሪያ ብር 16,375
ሎት 8 የሞንታርቦና ዲኮር አገልግሎት የጨረታ ማስክበሪያ ብር 16,375 ብቃት ያላቸውንና በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል።
በዚህም መሰረት፡-
- በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ በመንግሥት ግ/ን/አስ/ኤጀንሲ ድረ ገጽ ላይ በአቅራቢዎች ምዝገባ ዝርዝር የተመዘገቡ፣ የቲን እና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
- ተጫራቾች የጨረታው ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታው ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው
- ተጫራቾች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ዕለት አንስቶ በተከታታይ 10 የሥራ ቀናት በየሎቱ የማይመለስ ብር 300 በመክፈል በልደታ ክፍለ ከተማ ወ/6/ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 103 1ኛ ፎቅ በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያው ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት በወረዳው ቢሮ ቁጥር 103 1ኛ ፎቅ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት /11/ በአስራ አንደኛው ቀን በ4፡00 ታሽጎ በዕለቱ ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ይከፈታል። የመክፈቻ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ታሽጎ ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሳጥን ከመከፈቱ በፊት ለተወዳደሩባቸው ሎት-2 ሎት-3 ሎት-4 ሎት-5 ሎት-7 ናሙና ማቅረብ የሚኖርባቸው ሲሆን፤ በቀረበው የፍላጎት መግለጫ መሰረት የተሟላ የፍላጎት መግለጫ ማዘጋጀትና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን እቃዎች ለእያንዳንዱ ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል
- የዘገየ ጨረታና በጨረታ መክፈቻ ላይ ያልተነበበ ጨረታ ተቀባይነት የለውም
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፈባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈጻሚው መስሪያ ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለጨረታው ከቀረቡ የእቃዎች ዝርዝር ውስጥ መ/ቤቱ እስከ 20 በመቶ ለመጨመር ወይም ለመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- የቋሚ እቃ ሳንፕል በፎቶ የሚቀርብ ሆኖ እኛ በምናወጣው ስፔስፍኬሽን የሚታይ ይሆናል።
ልደታ ክፍለ ከተማ ወ6/-ፋ/ጽ/ቤት
ለተጨማሪ ማብራሪያ የመ/ቤቱ ስልክ ቁጥር፡- 0947903172
አድራሻ፡- ልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 6 አስተዳደር ብስራተ ገብሬል ወረድ ብሎ ውሃ ልማት አጠገብ ብሩክ
የሕክምና ማዕከል ፊት ለፊት ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አጠገብ ህንጻ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 103
በልደታ ክፍለ ከተማ ወ/6/አስተዳደር/ፋ/ጽ/ቤት
