ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወረዳ 01 ፋይናንስ ጽ/ቤት ከዚህ በታች በዝርዝር የተገለጹትን እቃዎች እና አገልግሎቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ።
የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቁጥር ወ-01-01-/2018
ሎት1. አላቂ የቢሮ ዕቃዎች፣ ሎት2. ልዩ ልዩ መሳሪያዎች፣ ሎት3 ማሸነሪ/ቋሚ እቃዎች፣ ሎት4 የደንብ ልብስ፤ ሎት5 የፅዳት ዕቃዎች፣ ሎት6 የህትመት አገልግሎት፣ ሎት7 የመስተንግዶ አገልግሎት፤ ሎት 8 የመኪና ኪራይ አገልግሎት፤ ሎት 9 የጉልበት አገልግሎት፣ ሎት 10 የቢሮ ቁሳቁስ ጥገና፣ ሎት 11 የኮምፒዩተር ጥገና፣ ሎት 12 - የዲኮር አገልግሎት፣ ሎት 13 የቢሮ ቁሳቁስ ቋሚ ዕቃ፣ ሎት 14 የመኪና ዕቃዎች፣ ሎት 15 የአትክልት ዘር፣ ሎት 16 የእንስሳት ህክምና መድኃኒቶች እና ቁሳቁስ
የኮ/ቀ/ክ/ከ/ወ01 ፋይናንስ ፅ/ቤት ከላይ በዝርዝር የተገለጹትን እቃዎች እና አገልግሎቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ። በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ አቅራቢዎች በጨረታ መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን፤
- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆን ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፣
- ተጫራቾች የንግድ ፈቃድ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥርና የቫት ተመዝጋቢነት የምስክር ወረቀት ሰነድ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ ማያያዝ አለባቸው።
- ከአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ መረጃቸው መገኘት የሚችል።
- ተጫራቾች ለመጫረት የሚፈልጉትን የጨረታ አይነት የዕቃዎች ናሙና በየሎቱ በማድረግ የሚያስፈልጉ ናሙናዎችን በሙሉ ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት ባሉት ቀናት ውስጥ ቦታው ድረስ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ለእያንዳንዱ ሎት1 ብር 6,000 /ስድስት ሺህ ብር/፣ ሎት2 ብር 5,000 /አምስት ሺህ ብር/፣ ሎት3 ብር 6,000 /ስድስት ሺህ ብር/፣ ሎት4 ብር 6,000 /ስድስት ሺህ ብር/፣ ሎት5 ብር 6,000 /ስድስት ሺህ ብር/፣ ሎት 6 ብር 4,000 /አራት ሺህ ብር/፣ ሎት7 ብር 5,000 /አምስት ሺህ ብር/፣ ሎት8 ብር 5,000 /አምስት ሺህ ብር/፣ ሎት 9 ብር 3,000 /ሶስት ሺህ ብር/፣ ሎት 10 ብር 6,000 /ስድስት ሺህ ብር/፣ ሎት 11 ብር 6,000 /ስድስት ሺህ ብር/፣ ሎት 12 ብር 5,000 /አምስት ሺህ ብር/፣ ሎት 13 ብር 6,000 /ስድስት ሺህ ብር/፣ ሎት 14 6,000 /ስድስት ሺህ ብር/፣ ሎት 15 3,000 /ሶስት ሺህ ብር/፣ ሎት 16 3.000 /ሶስት ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ /CPO ብቻ በየሎቱ በማሰራት ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ከላይ ከተዘረዘሩት የጨረታ ዓይነቶች በሙሉ ወይም በከፊል መጫረት ይችላሉ፡፡
- አንዱ በሰጠው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት አይቻልም ።
- ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት የሚችሉ አቅራቢዎች የጨረታውን ሰነድ ወደ አየር ጤና በሚወስደው መንገድ ከዘነበ ወርቅ አደባባይ ከፍ ብሎ የሚገኘው ወረዳ 01 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት አራተኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 402 ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት እስከ 10ኛው ቀን ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በየሎቱ በመክፈል መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች በ11ኛው ቀን የጨረታ ሰነድ የማይሸጥ መሆኑን እናሳውቃለን።
- ተወዳዳሪዎች የሚያቀርቡትን ሰነድ ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን ለየብቻ ኦርጅናል እና ኮፒ በማለት በፖስታ ላይ በመፃፍ በማሸግ ከላይ በተጠቀሰው ቢሮ ለዚሁ ጨረታ አገልግሎት በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 የስራ ቀናት ማስገባት አለባቸው።
- ጨረታው በ11ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ቀን ከጠዋቱ በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከላይ በተጠቀሰው ቢሮ ይከፈታል።
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም ካላንደር የሚዘጋው ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ታሽጎ በተጠቀሰው ቢሮ ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ በሚገዙበት ወቅት ሰነድ የሚሸጠው በየሎቱ ተለይቶ መሆኑን ማወቅ አለባቸው።
- አሸናፊው ማሸነፉ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ከ7 (ሰባት) የስራ ቀናት በኋላ የውል ማስከበሪያ ይዞ በመቅረብ ውል መዋዋል አለበት ካልቀረበ የጨረታ ማስከበሪያው ለመንግስት ገቢ ይሆናል።
- ጨረታው ከተዘጋ በኋላ የሚመጡ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት አይኖራቸውም።
- በጨረታው የሚሞላው ዋጋ ቫትን ያካተተ መሆን አለበት ከቫት ውጭ የተሞላ ዋጋ ተቀባይነት የለውም።
- ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን ከሰነድ ጋር በማያያዝ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ለመኪና ኪራይ አገልግሎት፣ ለጉልበት ስራ አገልግሎት፣ የንግድ ፈቃድ፣ የግብር መለያ ቁጥር፣ የንግድ ምዝገባ ብቻ ማሟላት ይኖርባቸዋል ።
- ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ :- በስልከ ቁጥር 011-348-66-08 /011369-42-06
ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወረዳ 01 ፋይናንስ ጽ/ቤት
