በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የበሻሌ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ዙር ጥቅል ግዥ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አውጥቶ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የበሻሌ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ዙር ጥቅል ግዥ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አውጥቶ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
|
ተ.ቁ |
የዕቃ ዝርዝር |
የጨረታ ማስከበሪያ ዋጋ |
|
ሎት1 |
አላቂ የትምህርት ዕቃ |
32,800 |
|
ሎት2 |
አላቂ የቢሮ እቃ |
10,000 |
|
ሎት3 |
የፅዳት ዕቃ |
24,000 |
|
ሎት4 |
ለህንፃ ቁሳቁስና ተገጣጣሚዎች መግዣ |
12,000 |
|
ሎት5 |
የደንብ ልብስ |
16,000 |
|
ሎት6 |
ለአላቂ የህክምና እቃ |
600 |
|
ሎት7 |
ህትመት |
3000 |
|
ሎት8 |
ፕላንትና ማሽነሪ መግዣ |
40,000 |
|
ሎት9 |
ልዩ ልዩ መሳሪያዎች እና መፃህፎች |
14,000 |
|
ሎት10 |
ለምርምር እና ለልማት አላቂ እቃዎች |
10,000 |
|
ሎት11 |
ለፐላንት ማሽነሪ እና መሳሪያ እድሳት ጥገና |
3,500 |
|
ሎት12 |
ለህንፃ ቁሳቁስ ጥገና |
5,000 |
ስለሆነም መስፈርቱን የሚያሟሉ ተጫራቾች ቀርበው መወዳደር ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩበት ህጋዊ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር ለመክፈላቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
- በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚ/ር በአቅራቢነት የተመዘገቡና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
- የታደሰ ንግድ ፋቃድ ያለው፡፡
- ተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች ከላይ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 4 የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከዋጋ ማቅረቢያ ኦርጅናል ሰነድ ጋር እያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር ከላይ የተዘረዘሩት እቃዎች ለእያንዳንዳቸው የዋጋ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ (C.P.O) ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል የበሻሌ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ፋይናንስ ቡድን መሪ ቢሮ ቁጥር 5 ድረስ በመቅረብ መግዛትና መጫረት ይችላሉ፡
- ተጫራቾች ዋጋ የሞሉበትን ሰነድ ኦርጅናልና ኮፒ ብለው በመለየትና በ 2 ፖስታ በማሸግ እንዲሁም የተጠቀሱትን ማስረጃዎች አሟልተው የበሻሌ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ፋይናንስ ቡድን መሪ ቢሮ ቁጥር 5 ውስጥ ለዚሁ ተበሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ እስከ 10ኛው የስራ ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በ10ኛው ቀን ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በር/መምህር ቢሮ ይከፈታል፡፡
- ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪቻቸው በቀኑ ባይገኙም ጨረታው የሚከፈት ይሆናል።
- በጨረታ አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ በማስያዝ ከት/ቤቱ ጋር የግዥ ውል ስምምነት መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፈል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ዕቃ ሳምፕል ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- አሸናፊ ድርጅቶች ያሸነፋዋቸውን ዕቃዎች በራሳቸው ትራንስፓርት ወደ መስሪያ ቤቱ የበሻሌ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ፋይናንስ ቡድን መሪ ቢሮ ድረስ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ላይ ቅሬታ ካላቸው የጨረታው አሸናፊው ከተለየበት ቀን ጀምሮ በ7 የሥራ ቀናት ውስጥ ቅሬታቸውን ለጨረታ ኮሚቴ በጽሁፍ ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ ሲያቀርቡ ቫት ያጠቃለለና ከላይ የተጠቀሱትን ማስረጃዎች አሟልተው የበሻሌ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ፋይናንስና ቡድን መሪ ቢሮ ቁጥር 5 ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ እስከ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ብቻ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ሁለት ተወዳዳሪዎች ለአንድ ዕቃ ተመሳሳይ ዋጋ ቢያቀርቡ ኮሚቴው በጥራት ወይም ሌላ የቴክኒክ መስፈርት በመጠቀም አሸናፊ ይለያል፡፡
- ሁሉንም መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቾች በዋጋ ወይም በጥራት አሸናፊው የሚለይ ይሆናል።
- መ/ቤቱ አሸናፊውን ተጫራች በሚመርጥበት ጊዜ የሚገዛውን ዕቃ ወይም አገልግሎት ብዛት ወይም መጠን እንደ አስፈላጊነቱ እስከ 20% ለመቀነስ ወይም ለመጨመር መበቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- አሸናፊው ድርጅት የግዥ መጠየቂያ ወይም (Purchese Order) ከደረሳቸው ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ማቅረብ የሚችሉና የሚወዳደሩባቸው ዕቃዎች እስቶክ ላይ ያሉ መሆን አለባቸው፡፡
- አነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት መጫረት የምትችሉት የንግድ ፍቃዳችሁን ኮፒ በማድረግ ይዛችሁ ማምጣት ስትችሉ ነው፡፡ (በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ በግዥ አፈፃጸም መመሪያ ላይ ለአነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት ባወጣው መመሪያ መሰረት ነው፡፡)
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0116 68 29 02/ 0116 67 91 63 ወይም በአካል በሻሌ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሰሚት ሳፋሪ ቦሌ ምድብ ችሎት ፍርድ ቤት አጠገብ ፋይናንስ ቡድን መሪ ቢሮ በመቅረብ መጠየቅ ይቻላል፡፡
በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የበሻሌ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት
