በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2018 በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን እቃዎች አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር አ/አ/ደ/ማ /ባ/እቃ/ግ/ጨ/01/2018
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2018 በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን እቃዎች አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
|
ሎት ቁጥር |
የሚገዛው የእቃ ዓይነት |
የጨረታ ማስከበሪያ (CPO) መጠን |
ምርመራ |
|
1 |
አላቂ የቢሮ እቃዎች |
15,000.00 |
|
|
2 |
የፅዳት እቃዎች |
10,000.00 |
|
|
3 |
ቋሚ አላቂ እቃዎች |
5,000.00 |
|
|
4 |
የቢሮ መስተንግዶ እቃዎች |
8,000.00 |
|
|
5 |
የዴይ ኬር እቃዎች |
4,000.00 |
|
|
6 |
የመኪና እቃዎች |
5,800.00 |
|
|
7 |
የኤሌክትሮኒክስ ጥገና አገልግሎት |
5,800.00 |
|
|
8 |
የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች |
5,800.00 |
|
|
9 |
የፕሪንተር እና የኮፒ ማሽን ቀለም |
120,000.00 |
|
|
10 |
የፈርኒቸር እቃዎች |
15,000.00 |
|
|
11 |
የታሸገ ውኃ እና የቢሮ መስተንግዶ |
25,000.00 |
|
|
12 |
የቢሮ ሰራተኞች የደንብ ልብስ |
25,000.00 |
|
|
13 |
የመድረክ ማስዋብ ስራ |
3,000.00 |
|
|
14 |
የአሉሚኒም በር ተንጠልጣይ ቁልፍ እና ጥገና አገልግሎት |
30,000.00 |
|
|
15 |
የህትመት ውጤቶች |
11,000.00 |
|
|
16 |
የመድረክ ዝግጅት አገልግሎት ኪራይ |
10,000.00 |
|
በዚህ መሰረት በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መመሪያዎች በማሟላት መወዳደር ይችላሉ፦
- በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ ስለመሆናቸው የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
- የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ቲን TIN ማቅረብ የሚችሉ
- የአቅራቢነት ምዝገባ ሰነድ ማቅረብ የሚችሉ፣
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው ቀን ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ከ2፡30-11፡00 ሰዓት ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት 8ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 08/15 በመቅረብ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ቴክኒካል ኦርጅናል እና ኮፒ እንዲሁም ፋይናሻል ኦርጅናልና ኮፒ በታሸገ ኢንቨሎፕ ለየብቻው በማቅረብ ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 /አስር/ ተከታታይ የስራ ቀናት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ግዥና ንብረት አ/ጠ/አ/ ዳይሬክቶሬት 9ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 09/22 ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- የሚቀርበው ዋጋ ማቅረቢያ ፊርማና ማህተም ከሌለው ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ናሙና የተጠየቀባቸው እቃዎች ጨረታው ከመከፈቱ በፊት የድርጅታቸውን ማህተም በማድረግ ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻው በተገኙበት 4፡00 ሰዓት ይከፈታል።
- ተጫራቾች በሚጫረቱበት እያንዳንዱ እቃ ጥራት በቴክኒክ ብቃታቸው ከተመረጡ በዋጋ የሚወዳደሩ ይሆናል።
- ጨረታው ከተዘጋ በኋላ የሚያቀርቡት የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብት የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- አ/አ አራዳ ክፍል ከተማ (ፒያሳ) ልዩ ስሙ እሪ በከንቱ ተብሎ በሚጠራው የኢትዮጵያ ስታቲስቲካል አገልግሎት ቢሮ አካባቢ እስጢፋኖስ መካሻ አማረ (EMA) ህንፃ 9ኛ ፎቅ፤ ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 011 562 2343 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን
