በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 9 የጄኔራል ታደሰ ብሩ ቁጥር 1 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለ2018 ዓመት አገልግሎት የሚውል ኦርጅናል አላቂ የቢሮ እቃዎች፣ የፅዳት እቃዎች፣ የደንብ ልብስ፣ የደንብ ልብስ ስፌት፣ የትምህርት እቃዎች፤ ቋሚ እቃዎች፣ የተለያዩ ጥገናዎች፣ ህትመቶች ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 01/2018
በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 9 የጄኔራል ታደሰ ብሩ ቁጥር 1 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለ2018 ዓመት አገልግሎት የሚውል ኦርጅናል አላቂ የቢሮ እቃዎች፣ የፅዳት እቃዎች፣ የደንብ ልብስ፣ የደንብ ልብስ ስፌት፣ የትምህርት እቃዎች፤ ቋሚ እቃዎች፣ የተለያዩ ጥገናዎች፣ ህትመቶች ለመግዛት ስለሚፈልግ ተጫራቾች ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርት ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
- በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው፤ ቲን ነምበር እና አቅራቢ ዝርዝር ውስጥ መመዝገብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ይህንኑ የሚገልፅ ማስረጃ ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒውን ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ ሰነድ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በጉለሌ/ክ/ከተማ ወረዳ 9 እንቁላል ፋብሪካ እምብልታ ሆቴል ከፍ ብሎ ከሚገኘው የጄኔራል ታደሰ ብሩ 1ኛ ደረጃ ቁጥር 1 ት/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 በእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡትን እቃ ጥራት ያለው ደረጃውን የጠበቀ ስለመሆኑ ናሙና ማቅረብ ባለባቸው ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች እቃዎችን ዝርዝር እና የጨረታ ማወዳደሪያ ሀሳብ ላይ ስማችሁን፣ ፊርማችሁና አድራሻችሁን ማስፈርና ማህተም በማድረግ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 የስራ ቀናት በጉለሌ/ክ/ከተማ ወረዳ 9 የጄኔራል ታደሰ ብሩ ኛ ደረጃ ቁጥር 1 ት/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 ለጨረታው በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ እስከ 10ኛው ቀን 10፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ማስታወቂያው በወጣበት በ11ኛው ቀን በ4፡00 በጄኔራል ታደሰ ብሩ 1ኛ ደረጃ ቁጥር 1 ት/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 ይከፈታል፡፡ የጨረታው መክፈቻ ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ወይም በዓል ቀን ከዋለ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተገለፀው ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ተጫራቾች በሰነድ የሰጡት ዋጋ መለወጥ፣ ማሻሻል ወይም ከውድድሩ እራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
- የማወዳደሪያ ዋጋ ቫትን ጨምሮ መሞላት አለበት፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ጠቅላላ ዋጋ ለሎት1 ብር 2,500 (ሁለት ሺህ አምስት መቶ ብር)፣ ለሎት2 ብር 3,000 (ሶስት ሺህ ብር)፣ ለሎት3 ብር 2,500 (ሁለት ሺህ አምስት መቶ ብር)፣ ለሎት4 ብር 1,000 (አንድ ሺህ ብር)፣ ለሎት5 ብር 1,500 (አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር)፣ ለሎት6 ብር 1,000 (አንድ ሺህ ብር)፣ ለሎት 7 1,000 (አንድ ሺህ ብር)፣ ለሎት8 1,500 (አንድ ሺህ አምስት መቶ)፣ ለሎት9 1,500 (አንድ ሺህ አምስት መቶ) በባንክ በተመሰከረለት CPO ብቻ ማቅረብ አለባቸው።
- መ/ቤቱ እንደአስፈላጊነቱ የእቃውን ብዛት 20% መጨመር ወይም 20% ከውሉ በፊት መቀነስ የሚችል መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- መ/ቤቱ የሚገዛውን ዕቃ እስከ 6 ወር ዋጋ ጭማሪ ሳይደረግ ተጨማሪ 25% ዕቃ ግዥ መፈፀም ይችላል።
- አሸናፊ ድርጅት ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቹ ያሸነፈውን እቃ የመ/ቤታችን ንብረት ክፍል ድረስ በራሱ ትራንስፖርት አምጥቶ ማስረከብ አለበት፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ከአገር ውስጥ አቅርቦት ጋር በሚወደዳር ጊዜ 3% ልዩ አስተያየት ይደረግላቸዋል፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0118278952
በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 9 የጄኔራል ታደሰ ብሩ 1ኛ ደረጃ ቁጥር 1 ት/ቤት
