ሳሪስ ጤና ጣቢያ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት እቃዎችን በግልጽ ጨረታ መለያ ቁጥር 01/2018 አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ሳሪስ ጤና ጣቢያ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት እቃዎችን በግልጽ ጨረታ መለያ ቁጥር 01/2018 አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
- ሎት 1 የሠራተኛ ደንብ ልብስ 4. ሎት 4 የተለያዩ የፅዳት እቃዎች
- ሎት 2 አላቂ የቢሮ መገልገያ መሳሪያዎች 5. ሎት 5 የተለያዩ መሳሪያዎች
- ሎት 3 የተለያዊ ህትመት ሥራዎች 6. ሎት 6 የኤሌክትሮኒክስ ጥገና ሥራዎች
- ሎት 7 የጥገና እቃዎች ግዥ እና 8. ሎት 8 ቋሚ የቢሮ እቃዎች
ከላይ የተዘረዘሩትን እቃዎች ላይ መጫረት የምትፈልጉ ተጫራቾች
- በዘርፉ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚገልፅ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣ የግብር ከፋይነት የምስክር ወረቀት ያላቸው፣ ጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ የምስክር ወረቀት ያላቸው፣ ቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልፅ የምስክር ወረቀት እነዚህን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት የጨረታ ሰነዱን ከሳሪስ ጤና ጣቢያ ከፋ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 35 የማይመለስ ብር 100.00 (መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር ከሚሞሉት ጠቅላላ ዋጋ ሎት 1 (ደንብ ልብስ) 22,000.00 (ሃያ ሁለት ሺህ ብር) ፤ ሎት 2 (አላቂ የቢሮ መገልገያ መሳሪያዎች 15,000.00 (አስራ አምስት ሺህ ብር) ሎት 3 (የተለያዩ ህትመት ሥራዎች)፤ 16,000.00 (አስራ ስድስት ሺህ ብር) ሎት 4 (የተለያዩ የፅዳት እቃዎች) 25,000.00 (ሃያ አምስት ሺህ ብር)፣ ሎት 5 (ልዩ ልዩ መሳሪያዎች) 6000.00 (ስድስት ሺህ ብር)፣ ሎት 6 (የኤሌክትሮኒክስ ጥገና) 7,200.00 (ሰባት ሺህ ሁለት መቶ ብር) ሎት 7 (የጥገና እቃዎች ግዥ) 4000.00 (አራት ሺህ ብር) እና ሎት 8 (ቋሚ የቢሮ እቃዎች) 52,500.00 (ሃምሳ ሁለት ሸህ አምስት መቶ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) በአድራሻችን ከጨረታ ሰነድ ጋር በፖስታ በማሸግ ማቅረብ አለባቸው::
- ተጫራቾች በዚህ ጨረታ ተወዳድረው አሸናፊ ከሆኑ የአሸነፈው ድርጅት የውል ማስከበሪያ ጠቅላላ 10% ለሥራ አፈፃጸም ዋስትና በቅድሚያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ከተጀመረበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው የሥራ ቀን አየር ላይ ውሎ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በዛኑ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸቸው ባሉበት ሳሪስ ጤና ጣቢያ ፋይናንስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 35 ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም የጨረታ ሂደት በተቀመጠው መሰረት ይካሄዳል፡፡ የጨረታ መዝጊያ እና መክፈቻ ቀን ዝግ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች ከመሥሪያ ቤቱ በገዙት የጨረታ ሰነድ ላይ ብቻ የዋጋ ዝርዝር ሞልተው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ለሚወዳደሩት እቃዎች ሣምፕል ሙሉ በሙሉ ጨረታ ከመከፈቱ በፊት ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሙሉ ሰነድ ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን በመለየት የመሥሪያ ቤታችሁን ማህተም በማድረግ እና በእያንዳንዱ ሰነድ ላይ ፊርማቸውን በመፈረም በታሸገ ፖስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ካደራጃቸው አካል የድጋፍ ደብዳቤ ሲኖራቸው የጨረታ ሰነድ፣ የውል ማስከበሪያ እና የቅድመ ክፍያ ዋስትና ማስያዝ አይጠበቅባቸውም። ከሀገር ውስጥ አቅራቢዎች ጋር በሚያደርጉት ውድድር 3% ልዩ አስተያየት ይደረግላቸዋል።
- ተጫራቾች ዋጋ ሲሞሉ ስርዝ ድልዝ ካለው የተሠረዘው እቃ ከጨረታ ውጪ ይሆናሉ፡፡
- ተጫራቾች ዋጋ ሲሞሉ መሥሪያ ቤቱ ባወጣው እስፔክ መሠረት ብቻ ነው፣ እስፔኩን በራሳቸው የቀየሩት እቃ ከጨረታ ውጭ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች ዋጋ ሲሞሉ ቫትን አካቶ መሆን አለበት፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- ሳሪስ 3F ፊት ለፊት ከሙኒክ ሆቴል አጠገብ
ስልክ፡- 0114-70-98-59/0114-70-79-77 ደውለው ይጠይቁ፡፡
በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ የሳሪስ ጤና ጣቢያ
