በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግስት ግዥ ቡድን አገልግሎት ለሚሰጣቸው መ/ቤቶች በ2018 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋቸውን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ነገሮች ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የግዥ መለያ ቁጥር 001/2018
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግስት ግዥ ቡድን አገልግሎት ለሚሰጣቸው መ/ቤቶች በ2018 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋቸውን በ14/አስራ አራት/ ሎት ማለትም፡- ሎት 1- የተለያዩ የህትመት ስራዎች፣ ሎት 2- የአገልግሎት ኪራይ፣ ሎት 3- የትራንስፖርት አገልግሎት፣ ሎት 4- የቢሮ መስተንግዶ፣ ሎት 5- የስጦታ ዕቃዎች፣ ሎት 6- የመኪና ጌጣጌጥ፣ ሎት 7- የአላቂ የቢሮ ዕቃዎች እና ሌሎች አላቂ ዕቃዎች፣ ሎት 8- የፅዳት ዕቃዎች፣ ሎት 9- የሠራተኞች ደንብ ልብስ እና ስፌት፣ ሎት 10 - ኤልክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ ሎት 11 - የጀነሬተር ጥገና እና ሰርቪስ፣ ሎት 12 - የጀነሬተር ኪራይ ሎት 13 - የከባድ መኪና ጥገና እና ሰርቪስ፣ ሎት 14- መጋረጃዎች ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ማንኛውም
- በዘርፉ ሕጋዊ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ፣ ንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው (ግብር ከፋይነት ምዝገባ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤ ከግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት አቅራቢነት ማስረጃ ያለው፣ አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ ተመዝጋቢ የሆነ፣
- በዘርፉ በገንዘብ ሚኒስቴር በተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ እንዲሁም በ2018 በጨረታ መሳተፍ የሚችሉ መሆናቸው ከሚመለከተው ግብር ሰብሳቢ አካል በጨረታ መሳተፍ እንዲችሉ የሚሰጥ የታደሰ የምስክር ወረቀት /ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ፡- ለእያንዳንዱ ሎት ከአጠቃላይ ለበጀት ዓመቱ ከተበጀተው በጀት ከ0.5-2% የተሰላ ነው። ህጋዊ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርት አሟልቶ በጨረታው መወዳደር ይችላል።
|
ሎት 1 |
ሎት 2 |
ሎት 3 |
ሎት 4 |
ሎት 5 |
ሎት 6 |
ሎት 7 |
ሎት 8 |
ሎት 9 |
ሎት 10 |
ሎት 11 |
ሎት 12 |
ሎት 13 |
ሎት 14 |
|
7,000 |
3,000 |
10,000 |
3,000 |
5,000 |
5,000 |
10,000 |
5,000 |
5,000 |
15,000 |
5,000 |
10,000 |
10,000 |
7,000 |
- በእያንዳንዱ ሎት ለብቻው በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ADDIS KETEMA SUB CITY ADMIN-STRATOIN PUBLIC SERVICE & HUMAN RESOURECE DEVELOPMENT OFFICE PURCHASING ADMINISTRATION SUPPORTIVE PROCESS በሚል ስም የተሰራ ሲፒኦ ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ አለባቸው።
- የድጋፍ ደብዳቤ ለጨረታ ማስከበሪያ የተፃፈ ከሆነ ለጨረታ ማስከበሪያ ብቻ ነው ሰነድ በነፃ እንዲወስዱ ተብሎ ከተፃፈ ለሰነድ መወስጃ ብቻ ነው የሚያገልግለው
- የድጋፍ ደብዳቤ ካደራጀው አካል የተፃፈ የድጋፍ ደብዳቤ ይዞ ሲመጡ በነፃ ይወስዳሉ አምራቾች/በጥቃቅንና አነስተኛ በተደራጁ ማህበራት/ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ በሚያመርቱት ምርት ላይ 3% አስተያየት ይደረግላቸዋል፡፡
- የሚታዘዘው የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ተቀባይነት የሚኖረው የሲፒኦ ቁጥር የሚታይ ከሆነ፣ የተጫራቹን ስም በግልፅ የሚነበብ ከሆነ፣ ሲፒኦ ጀርባ ላይ የባንኩ ማረጋገጫ ማህተም ያለው ከሆነ ብቻ ነው።
- ተጫራች የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 /አስር/ የሥራ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታውን ሠነድ በሥራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 በአ/ከ/ክ/ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የፋይናንስ ቡድን 6ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 605 መውሰድ ይችላሉ ፡፡
- በክፍል 6 ባዶ በቴከኒክ መመዘኛዎች ላይ ተሟልቶ፣ ተፈርሞ እና ማህተም ተደርጎ፣ በሁሉም ገጽ ላይ ተፈርሞ የድርጅቱ ማህተም ተደርጎ ሙሉ የጨረታ ሰነድ /መመሪያ/ ተመላሽ ይደረጋል
- የጨረታ ሰነዱ ቴክኒካል ዋናውን አንድ /1/ እና ፎቶ ኮፒ /1/ ፋይናንሺያል ሰነድ ዋናውን አንድ /1/ እና ፎቶ ኮፒ አንድ /1/ ለየብቻ በፖስታ ታሸጎ በድምሩ አራት /4/ ፖስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል ኦርጅናል/ኮፒ ቴክኒካል እና ፋይናንሺያል በሚል በፖስታው ላይ በመግለጽ/በመፃፍ ለዚሁ ተበሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን አ/ከ/ክ/ከተማ ፐብሊከ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግስት ግዥ ቡድን 6ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 605 ማስገባት ይኖርበታል፡፡
- የጨረታ ሰነድ ለመግዛት እና ፖስታውን ለማስገባት ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት እለት ጀምሮ እስከ 10ኛው የስራ ቀን ከቀኑ 11፡30 ድረስ በአዲስ ከተማ ከ/ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግስት ግዥ ቡድን 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 605 ማስገባት ይችላሉ በ11ኛው የስራ ቀን ጠዋቱ 3፡00 የጨረታው ሳጥን የሚታሸግ ሲሆን በዚሁ ቀን ጠዋቱ 3፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው ይከፈታል፤ ነገር ግን 11ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
ለተጨማሪ መረጃ፡- 011-8-27-99-79 / 011-8-95-92-23-በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል።
አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከግሩም ሆስፒታል ከፍ ብሎ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፕብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የፋይናንስ ቡድን፤ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 605
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግስት ግዥ ቡድን
