የአማራ ፓይፕ ፋብሪካ ኃላ/የተ/የግል ኩባንያ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ የሚገኝ ፋብሪካው ሲሆን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ነገሮች በብሔራዊ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር APF/12/2018/Local
የአማራ ፓይፕ ፋብሪካ ኃላ/የተ/የግል ኩባንያ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ የሚገኝ ሲሆን ፋብሪካው
- ሎት 1 ሸራ ገመድ ብዛት 2,000
- ሎት 2 የተለያዩ የቤተ ሙከራ ማሽኖች
- ሎት 3 የተለያዩ የማሽን መካኒካል እና ኤሌክትሪካል መለዋወጫዎች (ብዛትና ዓይነታቸው በጨረታ ሠነዱ ላይ የሚገለፅ)
- ሎት 4 Yellow Master Batch ብዛት 575 kg እና
- ሎት 5 Black Master Batch ብዛት 32,500 kg
- ሎት 6 Different Green House Sheet Raw Materials/ Additives (ዓይነታቸው በጨረታ ሰነዱ ላይ የሚገለፅ) በብሔራዊ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ በዘርፉ የተሰማሩ ተጫራቾች -
- ለ2017/18 በጀት ዓመት የታደሰ የሕጋዊነት ማረጋገጫ ሠነዶችን ማቅረብ አለበት፡፡
- ዝርዝር የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በፋብሪካው የፋይናንስ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 105 በመቅረብ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ ይችላል፡፡
- በአማራ ፓይፕ ፋብሪካ ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባህር ዳር ቅርንጫፍ በተከፈተው የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000013149996 ገንዘቡን ገቢ በማድረግ የባንከ ደረሰኙን በኢሜይል አድራሻችን amharapipefactory@gmail.com በመላክ የጨረታ ሠነዱን ሶፍት ኮፒ በኢ-ሜይል በማግኘት በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
- ተወዳዳሪ ድርጅቶች ለተወዳደረበት ዕቃ ያቀረበውን ጠቅላላ ዋጋ 2% በባንከ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲ.ፒ.ኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በፋብሪካው ስም በማሰራት የጨረታ ማስከበሪያ ማቅረብ አለባቸው፡፡ የባንክ ዋስትናው በባንኩ ባ/ዳር ቅርንጫፍ በኩል ስለትክክለኛነቱ ማረጋገጫ የተሰጠበት መሆን አለበት፡፡
- በሎት 2፡ 4፡ 5 እና 6 ላይ ለተገለፁት ዕቃዎች ዝርዝር የቴክኒክ መስፈርት በአንድ ላይ (Technical Bid Offer) በማለት ለብቻው ከዋጋ ማቅረቢያው (Financial Bid Offer) በመለየት በፖስታ በማሸግ (ዋና ወይም ቅጂ ብሎ በጽሑፍ በመለየት) ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በሎት 1 እና 3 ላይ ለተዘረዘሩት ዕቃዎች Technical Specification ቴክኒካል መስፈርት ለብቻው ማቅረብ አይጠበቅባቸውም ፡፡ ይሁን እንጂ በዋጋ መመሪያ ቅፅ መሠረት የእቃዎች መጠሪያ ስም (የምርት አይነት) Brand Name and Trade Name የመግለፅ ግዴታ አለባቸው።
- እንዲሁም ተጫራቾች ለሁሉም ሎቶች የመወዳደሪያ ዋጋቸውን (Financial Bid Offer) እና የጨረታ ማስከበሪያቸውን ለብቻው ከቴክኒክ መስፈርት በመለየት በፖስታ በማሸግ (ዋና ወይም ቅጂ ብሎ በጽሑፍ በመለየት) ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ15ኛው ቀን ቢሮ ቁጥር 206 ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት 8፡30 ይከፈታል፡፡
- 15ኛው ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም የሕዝብ በዓል ቀን ከሆነ የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይሆናል፡፡
- ፋብሪካው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 206 በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 09-35-98-37-29/09-18-70-18-26 መደወል ይችላሉ፡፡
አማራ ፓይፕ ፋብሪካ ኃላ/የተ/የግል ኩባንያ
ባህር ዳር
