የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን ከታች የተገለጹትን ስራዎችን ለማሰራትና እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 38/2018
የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን ከታች የተገለጹትን ስራዎችን ለማሰራትና እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
- ሎት 1፡- የኢትዮ ኩባ ፓርክን የላድስኬፕ ዲዛይን ፣ ሱፐርቪዥን እና ኮንትራት አድሚኒስትሬሽን ስራ ለማሰራት
- ሎት 2 ፡- የብሄረጽጌ ፓርክን የላድስኬፕ ዲዛይን ፣ ሱፐርቪዥን እና ኮንትራት አድሚኒስትሬሽን ስራ ለማሰራት
- ሎት 3 ፡- የሳር ማጨጃ ማሽን ለመግዛት
- ሎት 4 ፡- የግንባታ ጥገና ስራ ለማሰራት
- ሎት 5 ፡- የመኪና ጎማዎች እና እቃዎች ለመግዛት
- ሎት 6 ፡- የተለያዩ የችግኝ ዝግጅት ግብአቶች እና እቃዎች ለመግዛት
- ሎት 7 ፡- ሚክሰር፣ ስፒከር እና ድንኳን ለመግዛት
- ሎት 8 ፡- የፕሮዳክሽን ስራዎች ውል በማሰር ለማሰራት
- ሎት 9 ፡- የውሃ ፓምፖች ፣ ፋውንቴኖች፣ ሳር ማጨጃ ማሽኖችን እና ለተለያዩ ማሽነሪዎችን ውል በማሰር ለማስጠገን ይፈልጋል።
በመሆኑም የተጠቀሱትን መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራጮች ተጋብዘዋል።
- ተጫራቾች በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት በታክስ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፍኬት እና ስለግብር አከፋፈል የሚሰጥ ማስረጃ (clearance) ማቅረብ አለባቸው
- ተጫራቾች ለእያንዳዳቸው ለሎት አንድ እና ሁለት 100,000.00 (አንድ መቶ ሺ) ብር፣ ከሎት 2 እስከ ዘጠኝ ላሉት ለየእያንዳዳቸው ብር 50,000.00 (ሀምሳ ሺ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሲፒአ ወይም ባንክ ጋራንቲ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን ስም ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 500 /አምስት መቶ ብር/ መገናኛ ዘፍመሽ ፊት ለፊት ታሜጋዝ ህንጻ ላይ ሶስተኛ ፎቅ የፋይናንስ ዳይሬክትሬት ቢሮ ውስጥ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ አስር ተከታታይ የስራ ቀን ከጠዋት 2፡30 እስከ 11፡30 ሰዓት ድረስ በመቅረብ መግዛት ይቻላል።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ፋይናንሻል ዶክመንት ለብቻ እና ቴክኒካል ዶክመንት ለብቻ በማሸግ እና ሁለቱንም ለየብቻ ኮፒ በማድረግ በአራት ፖስታ በማሸግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሳጥኑ እስከሚታሸግበት ከ10ኛው ተከታታይ የስራ ቀን በኋላ ከአለው 11ኛው ቀን ጠዋት 4፡00 ድረስ ለዚህ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ በዚያው ቀን ጠዋት 4፡30 መገናኛ ዘፍመሽ ፊት ለፊት ታሜጋዝ ህንጻ ላይ ሶስተኛ ፎቅ በግዥና ንብረት ዳይሬክትሬት ቢሮ ውስጥ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል።
- የጨረታ መክፈቻው ቀን ቅዳሜና እሁድ ላይ የሚውል ከሆነ በቀጣዩ ሰኞ በተጠቀሰው ሰዓት ተዘግቶ የሚከፈት ይሆናል።
- ዘግይቶ የደረሰ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
- ኮርፖሬሽኑ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፡- ስልክ ቁጥር 0777619010 /0977246014 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎችና ፓርኮች አስተዳደር ኮርፖሬሽን
