በአራዳ ክፍለ ከተማ የመስከረም 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለ2018 ዓ.ም በጀት አመት የሚያስፈልገውን የሰራተኞች የደንብ ልብስ፣ አላቂ ቢሮ እቃዎች፣ የጽሕፈት መሣሪያዎች፣ የቤተ ሙከራ እቃዎች፣ አጋዥ መጽሐፍት፣ ልዩ ልዩ መሳሪያዎች፣ የሴቶችና ወንዶች ቆዳ ጫማ፣ የላፕቶፕ፣ ዴስክቶፕና ፕሪንተር ግዥ የፈርኒቸር ምርቶች ግዥ፣ ለህፃናት ማቆያ የሚሆን የተለያዩ መጫወቻዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የግልፅ ጨረታ ማስታወስቂያ
የጨረታ ቁጥር 002/2018
በአራዳ ክፍለ ከተማ የመስከረም 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለ2018 ዓ.ም በጀት አመት የሚያስፈልገውን የሰራተኞች የደንብ ልብስ፣ አላቂ ቢሮ እቃዎች፣ የጽሕፈት መሣሪያዎች፣ የቤተ ሙከራ እቃዎች፣ አጋዥ መጽሐፍት፣ ልዩ ልዩ መሳሪያዎች፣ የሴቶችና ወንዶች ቆዳ ጫማ፣ የላፕቶፕ፣ ዴስክቶፕና ፕሪንተር ግዥ የፈርኒቸር ምርቶች ግዥ፣ ለህፃናት ማቆያ የሚሆን የተለያዩ መጫወቻዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በጨረታው መካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን ሁኔታዎች በቅድሚያ ማሟላት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች በተሰማሩበት የሥራ መስክ የዘመኑን ግብር ለመክፈላቸው የታደሰ የንግድ ፈቃድ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
- የመንግስት ግዥ ጨረታ ላይ ለመሳተፍ የሚያስችል የተሟላ ማስረጃ ያላቸው።
- የቫት ተመዝጋቢ ለመሆናቸው የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች በታሸገ ኤንቨሎፕ የገዙትን ሰነድ ኦርጅናሉን እና ኮፒ ሞልተው ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የሰራተኞች የደንብ ልብስ፣ አላቂ ቢሮ እቃዎች፣ የጽሕፈት መሣሪያዎች የቤተ ሙከራ እቃዎች አጋዥ መጽሐፍት፣ ልዩ ልዩ መሳሪያዎች፣ የሴቶችና ወንዶች ቆዳ ጫማ፣ የላፕቶፕ፣ ዴስክቶፕና ፕሪንተር ግዥ፣ የፈርኒቸር ምርቶች ግዥ፣ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ዝርዝር የያዘ ሰነድ የማይመለስ 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ማግኘት ይችላሉ።
- የጨረታ ሰነዶቻቸውን ዝርዝር ተጽፎ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚያገለግል የመጫረቻ ዋጋ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ /ብር 3,000.00 /ሦስት ሺህ ብር/ በማስያዝ በመስከረም 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 5 ለዚሁ ስራ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ከጠዋቱ 2፡30-6፡30 እና ከ7፡30-11፡00 ሰዓት ድረስ ከመወዳደሪያ ሰነዶቻቸው ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- አሸናፊ ተጫራች ከአሸነፉ በኋላ የውል ማስከበሪያ 10% ማስያዝ አለባቸው።
- ጨረታው በወጣ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ በ4፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በት/ቤቱ ቢሮ ቁጥር 2 ይከፈታል።
- ሙሉ ከገዙት ጨረታ ሰነድ ውጭ ተሞልቶ የመጣ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
- በጨረታው ላይ ተንተርሶ ዋጋ መጨመር አይቻልም።
- ያቀረቡበት ዋጋ ቫትን ያካተተ መሆን አለበት።
- ተጫራቾች ለተወዳደሩበት ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ ተቋማት ራሳቸው አምርተው ገበያ የሚያቀርቡት ዕቃ ወይም ምርት ካልሆነ በስተቀር የተዘጋጁ ዕቃዎችን ገዝተው ካመጡ የሚወዳደሩበት እንደማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ መግዛት እና የውል ማስከበሪያ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች ስርዝ ድልዝ የማይነበብ ሰነድ ጨረታ ላይ ያልተነበበ የዋጋ ማቅረቢያ ተቀባይነት አይኖረውም።
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። እንዲሁም መ/ቤቱ ዕቃዎችን 20% መጨመረም ሆነ መቀነስ የሚችል መሆኑን እንገልፃለን።
ለተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ፡- ስ/ቁ 0118-68-13-56/57
አድራሻ፡- ግቢ ገብርኤል በስተጀርባ ባዕታ ክሊኒክ አጠገብ
በአራዳ ክፍለ ከተማ የመስከረም 2ኛ ደረጃ ት/ቤት
