በአብክመ በምስራቅ ጎጃም ዞን የባሶ ሊበን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ለ2018 በጀት አመት ለሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል፡- ሎት-1 የጽህፈት መሳሪያ፣ ሎት- 2 ኮምፒዩተር ተዛማች፣ ሎት- 3 የኮንስትራክሽን እቃዎች፣ ሎት-4 አሸዋ፣ ሎት-5 ሲሚንቶ፣ ሎት-6 የውጭ ፈርኒቸር፣ ሎት የሀገር ውስጥ ፈርኒቸር፣ ሎት -8 የመኪና ጎማ፣ ሎት-9 የመኪና እቃ፣ ሎት-10 ይፈልጋል።
ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በአብክመ በምስራቅ ጎጃም ዞን የባሶ ሊበን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ለ2018 በጀት አመት ለሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል፡- ሎት-1 የጽህፈት መሳሪያ፣ ሎት- 2 ኮምፒዩተር ተዛማች፣ ሎት- 3 የኮንስትራክሽን እቃዎች፣ ሎት-4 አሸዋ፣ ሎት-5 ሲሚንቶ፣ ሎት-6 የውጭ ፈርኒቸር፣ ሎት የሀገር ውስጥ ፈርኒቸር፣ ሎት -8 የመኪና ጎማ፣ ሎት-9 የመኪና እቃ፣ ሎት-10 ይፈልጋል። የስፖርት እቃዎች፤ ሎት -11 ያገለገለ የመኪና ጎማ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛትና መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ተጫራቾች
- ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና ፍቃዳቸውን ያሳደሱ፣
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸውና ማቅረብ የሚችሉ፣
- ግዥው ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺ ብር) በላይ ከሆነ በተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ የተመዘገቡና ለመመዝገባቸው የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
- ተጫራቾች ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሉ ማስረጃዎችን ፎቶ ኮፒ በማድረግ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ ከሎት-1 እስከ ሎት-10 1% /አንድ ፐርሰንት/ በመሂ- 1፣ በ CPO ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል። ሎት-11 የጨረታ ማስከበሪያ 5% /አምስት ፐርሰንት/ በመሂ-1፣ በCPO ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከሎት-1 እስከ ሎት-11 የማይመለስ 50 ብር ከፍለው መግዛት ይችላሉ።
- ይህ ግልፅ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከሎት-1 እስከ ሎት-11 በተከታታይ ለ15 ቀን በአየር ላይ ውሎ በ 16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥን ታሽጎ በዚሁ እለት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎች/ በተገኙበት በግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 3 በግልጽ ይከፈታል፡፡ ነገር ግን የመክፈቻ ቀኑ በዓል ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀናት የሚከፈት ይሆናል።
- በጨረታው አሸናፊ የሆነው ድርጅት አሸናፊነቱ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ከ5 ተከታታይ የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የውል ማስከበሪያ 10% በማስያዝ ውል መፈጸም አለበት፡፡በተገለጸው የጊዜ ገደብ ያልቀረበና ውል ያልፈጸመ እንደሆነ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙትን ገንዘብ መ/ቤቱ ውርስ ያደርጋል፡፡
- ውድድሩ በሎት ወይም በጥቅል ዋጋ የሚለይ በመሆኑ ተጫራቾች ሁሉንም መሙላት እና በዋጋ መሙያ ሰነዱ ላይ የድርጅቱን ማህተም፣ ስም እና ፊርማ ማድረግ ይኖርባቸዋል።
- አሸናፊው ያአሸነፈበትን ኦርጅናል እቃዎችን ጽ/ቤቱ ድረስ ማቅረብ ይኖርበታል።፡
- ተጫራቾች ዋጋ መሙውያው ላይ ምንም ዓይነት ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም፣ ስርዝ ድልዝ ካለው ፓራፍ መደረግ አለበት፡፡
- የባ/ሊ/ወ/ገ/ጽ/ቤት በጨረታው የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
- የመንግስት የግዥ መመሪያ አዋጅና ከላይ የተዘረዘሩትን ማዘዣዎች ያላሟላ ተጫራች ከውድድር ውጭ ይሆናል፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0582460316/0565 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
በአብክመ በምስራቅ ጎጃም ዞን የባሶ ሊበን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
