የሀላባ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በሀላባ ዞን ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች ለ2018 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውል አላቂና ቋሚ የቢሮ እቃዎች ግዥ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የሀላባ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በሀላባ ዞን ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች ለ2018 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውል አላቂና ቋሚ የቢሮ እቃዎች ግዥ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህ መሰረት
1. ሎት 1 አላቂ እና ሌሎች አላቂ ዕቃዎች
2. ሎት 2 የደንብ ልብስ
3. ሎት 3 ኤሌክትሮኒክስ
4. ሎት 4 ፈርኒቸር
5. ሎት 5 የተለያዩ (CC) ያላቸው ሞተሮች እና ኤሌትሪክ ሞተር ሳይክሎችን ይጨምራል
6. ሎት 6 የህትመት ስራ (ባነር፣ ባጅ፣ መታወቂያ፣ የቢሮ ማህተሞች፣ የኃላፊ የስም ቲተር፣ ሰርተፊኬት)
7. ሎት 7 የሀላባ የባህል አልባሳት የወንድ እና ሴት
8. ሎት 8 እስታንዳርዱን የጠበቀ የቢሮ መጋረጃ
9. ሎት 9 የመብራት ዕቃዎች
10. ሎት 10 የተለያዩ የፈረስ ጉልበት ያላቸው ጄነሬተሮች ስለዚህ
1. ተጫራቾች አግባብነት ያለው በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፍቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (Tin) ሰርተፊኬት እና የዘመኑ ግብር የተከፈለበት ማስረጃ (ታክስ ክሊራንስ) ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ እንዲሁም ተጨማሪ ማቅረብ ያለባቸው ሰነዶች በጨረታ ሰነዱ በተገለፀው መሰረት ይሆናል፡፡
2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት በ15 ተከታታይ የስራ ቀን ውስጥ የጨረታ ሰነዱን እያንዳንዱን በብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመግዛት መውሰድ ትችላላችሁ፡፡
3. ጨረታው በ16ተኛ ቀን የጨረታው ሳጥን 4፡00 ሰዓት ታሽጎ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ይሆናል ሆኖም ግን በመክፈቻው ቀን የተጫራቾች ያለመገኘት መምሪያው ጨረታውን ከመከፈት የሚያስተጓጉለው ነገር አይኖርም፡፡
4. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ለእያንዳንዱ ሎት ብር 5,000 /አምስት ሺህ ብር/ በባንክ ዋስትና በታወቀ ባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ (CPO) ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
5. የጨረታው አሸናፊ ያለቅድመ ሁኔታ 10% የውል ማስረከቢያ (CPO) ወይንም አንኮንዲሽናል ባንከ ጋራንት ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
6. የጨረታው መክፈቻ ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በቀጣይ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ጨረታው የሚከፈት ይሆናል፡፡
7. መምሪያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብት በህግ የተጠበቀ ነው።
የሀላባ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
