በደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የአሪ ዞን ፋይናንስና ፕ/ልማት መምሪያ የጽሕፈት መሣሪያ፣ የሕትመት ሥራ፣ የታሸገ መጠጥ ውሃ፣ የመኪና ጎማ እና መለዋወጫ ዕቃዎች፣ የምግብ መስተንግዶ እና ሪፍሬሽመንት፣ የባሕል አልባሳት ግዥ፣ የኤልክትሮኒክስ እና ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የአሪ ዞን ፋይናንስና ፕ/ልማት መምሪያ የጽሕፈት መሣሪያ፣ የሕትመት ሥራ፣ የታሸገ መጠጥ ውሃ፣ የመኪና ጎማ እና መለዋወጫ ዕቃዎች፣ የምግብ መስተንግዶ እና ሪፍሬሽመንት፣ የባሕል አልባሳት ግዥ፣ የኤልክትሮኒክስ እና ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በማሟላት መወዳደር ይችላሉ፡፡
በሁሉም መስኮች ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ፍቃድ ያሳደሱ፡፡ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (tin number) እና ተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሠርተፍኬት (VAT) ማስረጃ ያለው፤ የንግድ የምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችል እንዲሁም የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና፣ የጽሕፈት መሣሪያ፤ የታሸገ መጠጥ ውሃ ፤ ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች እና የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች 10,000 ብር ብቻ ማቅረብ አለባቸው።
ከላይ የተገለጹን ኮፒ ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ የሚችሉ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 የሥራ ቀናት ውስጥ የጨረታ ሰነድ በነፃ ከኣሪ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ከግዥ/ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 12 ቀርቦ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ። የጨረታውን ሰነድ በ16ኛው /አስራ ስድስተኛው/ የሥራ ቀን ከሆነ ብቻ ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 እስከ 6፡30 ሰነዱን አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ኮፒ በአንድ እናት ፖስታ በማሸግ ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ገቢ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በዚያው ቀን 8፡30 ሰዓት ባለቤቱ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ጨረታው ሲከፈት የተጫራቾች ያለመሟላት የጨረታ ሂደቱን አያስተጓጉልም።
መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በደ/ኢ/ክልል ኣሪ ዞን ፋይናንስና ፕ/ልማት መምሪያ ጂንካ
