የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ እቃዎችን፣ የሰራተኞች የደንብ ልብስን፣ የተለያዩ የህትመት ስራዎችን እና የደህንነት መጠበቂያ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
ብሔራዊ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 002/2018
የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ እቃዎችን፣ የሰራተኞች የደንብ ልብስን፣ የተለያዩ የህትመት ስራዎችን እና የደህንነት መጠበቂያ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
|
ሎት |
የሚገዛው ዕቃ/አገልግሎት |
የጨረታ ማስከበሪያ /ሲፒኦ |
|
ሎት 1 |
የደንብ ልብስ እና የደህንነት መጠበቂያ ዕቃዎች |
20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) |
|
ሎት 2 |
አላቂ የጽህፈት መሳሪያዎች |
20,000.00 (ሃያ ሺ ብር) |
|
ሎት 3 |
ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች |
50,000.00 (ሃምሳ ሺህ) |
|
ሎት 4 |
የተሽከርካሪ ጎማ |
20,000.00 (ሃያ ሺህ) |
|
ሎት 5 |
የጽዳት ዕቃዎች |
10,000.00 (አስር ሺህ) |
|
ሎት 6 |
የተለያዩ የህትመት ስራዎች |
10,000.00 (አስር ሺህ) |
ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው፡-
1. በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ያላቸው፣
2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣
3. የተጨማሪ እሴት ታክስ /የቫት/ ተመዝጋቢ መሆናቸውን ማቅረብ የሚችሉ፣
4. የአቅራቢነት ሰርተፊኬት ያላቸው እና የግብር መክፈያ መለያ ቁጥር /Tin No/ ያላቸው
5. ተጫራቾች በባንክ የተረጋገጠ በመ/ቤታችን ስም የተዘጋጀ CPO ወይም ቅድመ ሁኔታ የሌለው የባንክ ዋስትና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን መግዛት የሚችሉት ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ብቻ ይሆናል፡፡
7. በጨረታ ማስታወቂያው የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ማንኛውም ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የሥራ ቀናት ሰነዱን ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 300 (ሦስት መቶ) በመክፈል ዘወትር በስራ ሰዓት ቃሊቲ ማሰልጠኛ አካባቢ በሚገኘው የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት ስም በተከፈተ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000493810317 ገቢ በማድረግ የባንክ ዲፖዚት ስሊፕ አሪጅናል በመያዝ መግዛት ይችላሉ፡፡
8. አሸናፊው ድርጅት ጥራቱን የጠበቀ ዕቃ አገልግሎት ካላቀረበ በራሱ ወጪ የመለወጥ ግዴታ አለበት፣
9. ድርጅቱ ካቀረበው ሰነድ ውጪ በሌላ ሰነድ በአማራጭነት ማቅረብ አይቻልም፣ ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ቴክኒካል ኦርጅናል እና ኮፒ እንዲሁም ፋይናንሽያል ኦርጅናል እና ኮፒ ለየብቻ በፖስታ አሽገው የድርጅታቸውን ማህተምና ፊርማ በማድረግ ለጨረታ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፣
10. ተጫራቾች ናሙና እንዲቀርብባቸው ለተጠየቁ እቃዎች ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ናሙና ያላቀረበ ተጫራች ከጨረታ ውድድር ውጪ ይሆናል፡፡
11. ተጫራቾች መ/ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ዋጋ ላይ ስርዝ ድልዝ ሳይኖርበት በትክክል መሙላት አለባቸው፤
12. ከጥቃቅንና አንስተኛ የሚመጡ ተጫራቾች ለምትጫረቱባቸው ዕቃዎች የጨረታ ሰነዱን በነጻ ለመውሰድ
ሀ. ካደራጃችሁ መ/ቤት ደብዳቤ ማምጣት አለባቸው፣
ለ. ሰነዱን በነጻ መውሰድ የምችሉት በመመሪያ መሰረት ለምትወደደሩበት ዕቃ አምራች መሆን አለባቸሁ፣ ጨረታው ከተከፈተ በኋላ አሸናፊው ድርጅት ያሸነፈበትን ዕቃ ወይም አገልግሎት ዝርዝር ላይ የጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡ እንዲሁም አሸናፊ የሆነው ድርጅት አሸናፊነቱ በደብዳቤ እንደተገለፀለት በመ/ቤታችን ቀርቦ ውል መዋዋል አለበት ይህ ባይሆን ግን ለዋስትና ያስያዘው የጨረታ ማስከበሪያ ገንዘብ ለመንግስት ገቢ ይሆናል፡፡
13. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በጋዜጣ ከወጣበት ከ15 ተከታታይ የስራ ቀናት በኋላ በ16ኛው ቀን ጧት 4፡00 ታሽጎ ወዲያው በ4፡30 ይከፈታል። ነገር ግን 16ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን ላይ በተጠቀሰው ሰዓት የሚከፈት ይሆናል።
14. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ስ.ቁ 0114708116
የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት
