አክሽን ፎር ዴቬሎፕመንት /ACTION FOR DEVELOPMENT/ ያገለገሉ ቀላል ተሸከርካሪዎች ሞተር ሳይክሎች፣ እንዲሁም የተለያየ ዓይነት ያገለገሉ የቢሮ ዕቃና የቢሮ የሥራ መሣሪያዎችን ባሉበት ሁኔታ በዝግ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር AFDAO-30/2026
አክሽን ፎር ዴቬሎፕመንት /ACTION FOR DEVELOPMENT/ ያገለገሉ ቀላል ተሸከርካሪዎች ሞተር ሳይክሎች፣ እንዲሁም የተለያየ ዓይነት ያገለገሉ የቢሮ ዕቃና የቢሮ የሥራ መሣሪያዎችን ባሉበት ሁኔታ በዝግ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ስለሆነም፡-
ሀ. ተሸከርካሪዎቹንና ሞተር ሳይክሎቹን መግዛት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች የማይመለስ ብር 300.00 (ሦስት መቶ ብር) በመክፈል፤
ለ. የቢሮ ዕቃዎችንና የቢሮ የሥራ መሣሪያዎችን መግዛት የሚፈልግ ተጫራች የማይመለስ ብር 300.00 (ሦስት መቶ ብር) በመክፈል፣
ሐ. በፊደል ተ/ቁ. "ሀ" እና "ለ" የተጠቀሱትን መግዛት የሚፈልግ ተጫራች ደግሞ፤ ለሁለቱም የማይመለስ ብር 600.00 (ስድስት መቶ ብር) በመክፈል፣
ለእያንዳንዳቸው የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ (የጨረታ ዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ) 22 ማዞሪያ ከጎላጎል ህንፃ ወደ ቦሌ መድሃኒ ዓለም በሚወስደው መንገድ ከቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል 100 ሜትር ወረድ ብሎ ወደ ቀኝ በሚታጠፈው መንገድ በመጓዝ ከቅዱስ ማርቆስ ት/ቤት ፊት ለፊት ሲደርሱ ወደ ግራ 50 ሜትር ገባ ብሎ ከሚገኘው የድርጅቱ ግዢ ክፍል በመውሰድ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ፡-
1. ለጨረታ የቀረቡትን ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችና ሞተር ሳይክሎች እንዲሁም የቢሮ ዕቃዎችና የቢሮ የሥራ መሣሪያዎችን ከላይ በተጠቀሰው የድርጅቱ ዋናው መ/ቤት ቅጥር ግቢ በአካል ተገኝቶ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ መመልከት ማየት ይችላል።
2. ለተሸከርካሪዎችና ሞተር ሳይክሎች ግዢ ተጫራቹ የሚያቀርበውን ዋጋ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ቁጥር "ADAO-30/A" "የተሽከርካሪዎችና ሞተር ሳይክሎች የጨረታ ዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ ላይ በመሙላት በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ ውስጥ አስገብቶ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከላይ በተጠቀሰው የድርጅቱ አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይችላል።
3. ለቢሮ ዕቃዎችና ለቢሮ የሥራ መሣሪያዎች ግዢ ተጫራቹ የሚያቀርበውን ዋጋ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ቁጥር "AEDAO-30/B" "የቢሮ ዕቃዎችና የቢሮ የሥራ መሣሪያዎች የጨረታ ዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ ላይ በመሙላት በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ ውስጥ አስገብቶ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከላይ በተጠቀሰው የድርጅቱ አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይችላል።
4. እያንዳንዱ ተጫራች ለሚጫረትበት ተሽከርካሪና ሞተር ሳይክል እንዲሁም የቢሮ ዕቃና የቢሮ የሥራ መሣሪያዎች የጨረታ መነሻ ዋጋ ግምታቸውን 10% የጨረታ ማስከበሪያ (ቢድ ቦንድ) በባንከ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ ሰነድ (CPO) በአከሽን ፎር ዴቬሎፕመንት /ACTION FOR DEVELOPMENT/ ድርጅት ስም አሠርቶ ከጨረታው ሰነድ ጋር በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ ውስጥ በማስገባት ማቅረብ አለበት። በሚያስገቡት ፖስታ ላይም የተጫራቹ ሙሉ ስምና አድራሻ መገለፅ ይኖርበታል።
5. ሌሎች ተጫራቾች ባቀረቡት ወይም በሰጡት ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት የተከለከለ ነው።
6. ጨረታው ለተሸከርካሪዎችና ሞተር ሳይክሎች መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ/ም እንዲሁም ለቢሮ ዕቃዎችና ለቢሮ የሥራ መሣሪያዎች ደግሞ፣ መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ በድርጅቱ ዋናው መ/ቤት መገኘት በሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ፊት ይከፈታል።
7. ከጨረታው ሳጥን መዝጊያ ቀንና ሰዓት በኋላ፣ የሚቀርቡ ማናቸውም የመወዳደሪያ መጫረጫ ሰነዶች ተቀባይነት አይኖራቸውም።
8. ያለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) የሚቀርብ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት አይኖረውም።
9. በጨረታው ለተሸነፉ ያስያዙት የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ /ቢድ ቦንድ/ የጨረታው የግምገማ ውጤት ከተገለፀ በኋላ፣ የሚመለስላቸው ሲሆን፣ የጨረታው አሸናፊዎች ደግሞ፣ ያስያዙት ገንዘብ ለሚገዙት ንብረት ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር ይታሰብላቸዋል።
10. የጨረታው አሸናፊ የጨረታው ውጤት ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ7 ቀናት ውስጥ ያሸነፈበትን ገንዘብ አጠናቅቆ በመክፈል ተሸከርካሪዎቹን፣ ሞተር ሳይክሎቹንም ሆነ ሌሎች በጨረታ ያሸነፈባቸውን ንብረቶች አሸናፊነቱ ከተገለፀበት እስከ 10ኛው ቀን ድረስ ሙሉ በሙሉ ማንሳት አለበት፤ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ካላነሳ የጨረታው ውጤት ተሰርዞ ያስያዘው ገንዘብ በቅጣት መልክ ለድርጅቱ ገቢ ይሆናል።
11. አሸናፊ ተጫራቾች የገዙትን ተሸከርካሪም ሆነ ዕቃ በራሳቸው ወጪ አስነስተው ይወስዳሉ።
12. አሸናፊ ተጫራቾች ከስም ዝውውር ጋር በተያያዙ የሚደረጉ ክፍያዎችን፤ የመንግስት ቀረጥ ታከስ እንዲሁም ማንኛውንም ተዛማጅ ወጪዎችን ይሸፍናሉ፡፡
13. ድርጅቱ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-662-59-76/0939655371 በመደወል ወይም ከላይ በተጠቀሰው የድርጅቱ አድራሻ በግንባር ቀርቦ መጠየቅ ይቻላል።
አክሸን ፎር ዴቬሎፕመንት
