የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ያገለገሉ የተለያዩ ዓይነት የመኪና መለዋወጫ ዕቃዎች፣ የተለያየ አይነት ያገለገለ የቢሮ እቃዎች፣ ቁርጥራጭ እንጨቶች፣ የተለያዩ ዓይነት ያገለገሉ የመኪና እና የሞተር ሳይክል ጎማዎች፣ የተለያዩ አይነት ቶነሮች፣ ያገለገሉ የመኪና ባትሪ፣ የተለያዩ ጀሪካኖች፣ ለስላሳ መጠጦች፣ ቬንትሌተሮች እና ያገለገሉ በሮች፣ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈል
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
ያገለገሉ የተለያዩ ንብረቶች የግልፅ ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ያገለገሉ የተለያዩ ዓይነት የመኪና መለዋወጫ ዕቃዎች፣ የተለያየ አይነት ያገለገለ የቢሮ እቃዎች፣ ቁርጥራጭ እንጨቶች፣ የተለያዩ ዓይነት ያገለገሉ የመኪና እና የሞተር ሳይክል ጎማዎች፣ የተለያዩ አይነት ቶነሮች፣ ያገለገሉ የመኪና ባትሪ፣ የተለያዩ ጀሪካኖች፣ ለስላሳ መጠጦች፣ ቬንትሌተሮች እና ያገለገሉ በሮች፣ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ከጨረታ ሰነዶች ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
1. የእቃዎቹ ዓይነትና ዝርዝር በጨረታው ሰነድ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ይህ ማስታወቂያ በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ አስር /10/ ቀናት ውስጥ ጨረታ ሰነዱን በጉርድ ሾላ ሳሊተ ምህረት ቤ/ክርስቲያን ፊት ለፊት ድራር ሞል አጠገብ ከሚገኘው ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በመገኘት የጨረታውን ዝርዝር መረጃ የያዘውን የጨረታ ሰነድ በብር 800 /ስምንት መቶ ብር/ በመግዛት የጨረታ ሰነዳችሁን እስከ ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ሰዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
2. የእቃዎቹን ዓይነትና ዝርዝር ሁኔታ በአካል ማየት የሚፈልጉ በጉርድ ሾላ ሳሊተ ምህረት ቤ/ክርስቲያን ፊት ለፊት ድራር ሞል አጠገብ የሚገኘው በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በግምጃ ቤት በመገኘት ጨረታው በሪፖርተር በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሰነዱን የገዙ ተጫራቾች ብቻ መጎብኘት ይችላሉ፡፡
3. ተጫራቾች ከጨረታው በኋላ የሚመለስ የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ ለሚጫረቱበት ጠቅላላ ዋጋ ሁለት በመቶ /2%/ /CPO/ ወይም ባንክ ጋራንቲ አያይዞ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
4. ገዥዎች የሚገዙበትን ዋጋ በታሸገ ኤንቬሎፕ እስከ ጨረታ መዝጊያ ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. 8:00 ሰዓት ተዘግቶ በአስቱ 8:30 በጉርድ ሾላ በሚገኘው ሳሊተ ምህረት ቤ/ክ ፊት ለፊት ድርራ ሞል አጠገብ በሚገኘው የማኀበሩ መሰብሰበያ አዳራሽ ውስጥ ተጫራቾች ወደም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
5. ተጫራቾች ጨረታውን አሸናፊ መሆናቸው ከተገፀላቸው ተጫራቾች የሸነፉትን ንብረት ሙሉ ክፍያውን በአምስት ቀናት ውስጥ ክፍለው ማንሳት ይኖርበቸዋል። ካልሆነ ግን ጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ሲፒኦ /Cpo/ ድርጅቱ ገቢ ያደርጋል ወይም ተመላሽ አይሆንም፤
6. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ተጫራቾች ስለጨረታው ተጨማሪ ማብራሪያ ሲፈልጉ ከዚህ በታች በተጠቀሰዉ አድራሻ ስልክ በመደወል ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር
አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ ቤት
ስልክ ቁጥር: 011-515-06-08
ፖስታ ሳጥን ቁጥር: 41076
