Tender Detail

Tender Details


በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሚዳ ወረሞ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለወረዳው ሴክተር መ/ቤቶች ለ2019 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ1ኛ የጽ/መሳሪያ 22000 ብር 2ኛ የመኪና እቃ መለዋወጫ 40000 ብር 3ኛ/ የእንስሳት መድሃኒት 20000 ብር 4ኛ የፕሪንተር ቀለም 15000 ብር 5ኛ/ የጽዳት እቃ 8000 ብር 6ኛ ጎማና ከለመዳሪ 15000 ብር 7ኛ ቋሚ የቢሮ እቃ 10000 ብር 8ኛ ህትመት 12000


በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

 

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሚዳ ወረሞ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለወረዳው ሴክተር መ/ቤቶች ለ2019 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ1ኛ የጽ/መሳሪያ 22000 ብር 2ኛ የመኪና እቃ መለዋወጫ 40000 ብር 3ኛ/ የእንስሳት መድሃኒት 20000 ብር 4ኛ የፕሪንተር ቀለም 15000 ብር 5ኛ/ የጽዳት እቃ 8000 ብር 6ኛ ጎማና ከለመዳሪ 15000 ብር 7ኛ ቋሚ የቢሮ እቃ 10000 ብር 8ኛ ህትመት 12000 ብር 9ኛ የውሃ እቃ 15000 ብር 10ኛ የስፖርት ትጥቅና ማቴሪያል 20000 ብር በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታ እንዲሳተፉ ይጋብዛል።

1.    በዘርፉ የታደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር /ቲን እንዲሁም በጨረታ ሰነዱ ላይ የሚሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ ድምር ከብር 200,000/ ሁለት መቶ ሺህ ብር / በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢነት ማስረጃ ኮፒ ማቅረብ የሚችሉ።

2.    ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ የጨረታ ሰነድ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ እስከ 15ኛው ቀን ከቀኑ 11፡30 ድረስ የማይመለስ 1000 /አንድ ሺህ ብር/ በመክፈል በሚዳ ወረሞ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 6 ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።

3.    ተጫራቾች በተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ላይ ስርዝ ድልዝ ሳይኖረው የነጠላ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ ሞልተው ኮፒና ኦርጅናል ሰነድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

4.    ተጫራቾች በተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ላይ የጠቅላላ ዋጋ በዝርዝር ተሞልቶ ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ከላይ በተዘረዘረው ሎት የገንዘብ መጠን የጨረታ ማስከበሪያ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸው የታወቁ ባንኮች የሚሰጥ ሲ.ፒ.ኦ /C.PO/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በባንክ የተረጋገጠ ሌተር ኦፍ ክሬዲት ወይም በጥሬ ገንዘብ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

5.    ተጫራቹ በዋጋ መሙያ ሰነድ ላይ ስም ፊርማና ማህተም በማድረግ በታሸገ ፖስታ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛ ቀን 3፡30 ድረስ በሚዳ ወረሞ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

6.    የጨረታ አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ዕቃውን በሚ/ወ/ወ/ሴክተር መ/ቤቶች ባሉት ንብረት ክፍል ውስጥ ማድረስ ይኖርባቸዋል።

7.    የጨረታ ውድድሩ እንደአስፈላጊነቱ በነጠላ ዋጋ ወይም በሎት ሊሆን ይችላል።

8.    ጨረታው ተጫራቾች በአካልም ሆነ ህጋዊ ወኪሎቻው በተገኙበት ወይም ባልተገኙበት በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ታሽጎ ከጠዋቱ 4፡00 በሚዳ ወረሞ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 18 ይከፈታል። የመክፈቻ ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ላይ የጨረታ ሰነድ የመጨረሻ ማስገቢያ ከጠዋቱ 3፡30 ሆኖ ከጠዋቱ 4፡00 ላይ ጨረታው ይከፈታል።

9.    መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ ስ/ቁ 09 22 88 42 72 ወይም 09 13 57 44 40 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ። 

በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን የሚዳ ወረሞ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

✨ messages.ai_summary
- The Mida Woromo District Finance Office in North Shewa Zone, Amhara Region, is procuring 10 categories of supplies for district sector offices for the 2019 budget year: office stationery (22,000 ETB), vehicle spare parts (40,000 ETB), animal medicine (20,000 ETB), printer ink (15,000 ETB), cleaning supplies (8,000 ETB), tires and tubes (15,000 ETB), fixed office equipment (10,000 ETB), printing (12,000 ETB), water supplies (15,000 ETB), and sports equipment and materials (20,000 ETB). - Bid documents cost a non-refundable 1,000 ETB and may be purchased until the 15th day at 11:30 AM from the Mida Woromo District Finance Office, Room No. 6. - Bids close on the 16th day at 3:30 PM and open at 4:00 PM at the Mida Woromo District Finance Office, Room No. 18. - Bid bond amounts vary by lot and must be submitted as CPO, an unconditional bank guarantee, a bank-confirmed letter of credit, or cash from National Bank of Ethiopia-approved banks. - Bidders must hold a renewed trade license, paid current taxes, a TIN, and VAT registration proof if the total price exceeds 200,000 ETB; winning bidders must deliver goods to the sector offices' property department.
Save Tender