Tender Detail

Tender Details

  • Company በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የወረዳ 5 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት
  • Address ከመድሃኒዓለም ት/ቤት ወደ አበበ ቢቂላ ስታዲየም መውረጃ 300 ሜትር ገባ ብሎ : አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 011-8-27-81-54
  • Website
  • Deadline07 Sep 2026, 10:00 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Price200.00 /ሁለት መቶ/ ብር
  • opening dateበ11ኛው የስራ ቀን 4፡30 ሰዓት
  • Categories Furniture And Furnishing , Cleaning & Janitorial , Office Supplies And Services

በአ/ከ/ክ/ ከተማ የወረዳ 5 ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት ለተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል።


1ኛ ዙር ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር፣ አ/ከ/ክ/ከ/ወ/5/ፋ/ጽ/001/19

 

በአ/ከ/ክ/ ከተማ የወረዳ 5 ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት ለተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል።

ሎት ቁጥር

 

የሎት ዝርዝር

 

ከጠቅላል ዋጋ የሚያሲዙት/የብር መጠን/

 

ሎት 1

 

የደንብ ልብስ

 

27,234.85

 

ሎት 2

 

ቋሚ ዕቃዎች

 

5,000.00

 

ሎት 3

 

የቢሮ የጽህፈት መሳሪያዎች

 

15,448.42

 

ሎት 4

 

የፅዳት ዕቃዎች

 

18,469.14

 

ሎት 5

 

የቢሮ መስተንግዶ

 

22,648.8

 

ሎት 6

 

የመኪና ኪራይ

 

14,593.59

 

ሎት 7

 

የተለያዩ የዲኮር ስራዎች

 

5,003.75

 

ሎት 8

 

የጉልበት ሰራተኛ

 

5,250.00

 

ሎት 9

 

የሕትመት ስራዎች

 

1000.00

 

ሎት 10

 

የደንብ ልብስ ስፌት

 

10,000.00

 

ሎት 11

 

የተለያዩ የግብርና ዘሮች

 

4,500.00

 

ሎት 12

 

የሰራተኞች መዝናኛ ክበብ

 

22,648.8

 

 

በመሆኑም ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶችን የምታሟሉ ተጫራቾች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል።

*        የዘመኑን ግብር ከፍለው የታደሰ ንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉና የግብር መለያ ቁጥር ያላቸው።

*        የቫት/TIN NO/ ተመዝጋቢ የሆኑና በአቅራቢዎች ዝርዝር በዌብ ላይት ስለመመዝገባቸው መረጃ የምናይ መሆኑን

*        ተጫራቾች ለመወዳደር የጨረታ ሰነድ ስታስገቡ ለተወዳደራችሁበት አላቂ ዕቃ እና የልብስ ስፌት ሳምፕል ማቅረብ ይኖርባችኋል።

*        ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ /cpo/ ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ 0.5% በማስላት በማስያዝ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ይህን ካላቀረቡ ከውድድር ውጪ ይሆናሉ።

*        ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት በማይመለስ ብር በካሽ 200.00 /ሁለት መቶ/ ብር በመክፈል በወረዳ 5 ፋ/ጽ/ቤት 2ተኛ ፎቅ ወደ ቢሮው ሲገቡ በስተቀኝ በመግባት መግዛት ይችላሉ።

*        የጨረታ ሠነዱ በተጫራቾች መሞላት ያለባቸው ከፍሎች በሙሉ መሞላት አለባቸው።

*        በስራ ኢንተርፕራይዝ የተደረጃችሁ በራሳችሁ ምርት ላይ ልዩ አስተያየት ስለሚደረግ አምራች መሆናችሁን የሚገልፅ መረጃ ካደራጃችሁ አካል የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ አለባችሁ።

*        በስራ ኢንተር ፕራይዝ የተደራጃችሁ ከምታመርቱት ምርት ውጪ ባለ ዘርፍ እና ሰነድ ላይ እንደማንኛውም ተጫራች ድርጅት cpo ማስያዝ ይኖርባችኋል።

*        ለሰራተኞች ካፍቴርያ መብራት ክፍያ በወር 4,000 ውሃ የቤት ኪራይ 'የመስሪያ ቁሳቁሶች ከመ/ቤቱ የሚቀርብ ይሆናል።

*        ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ ሲያቀርቡ ቫትን አካተው ዋናውንና ኮፒውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።

*        ጨረታው በ11ኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 4፡30 ይከፈታል።

*        ጨረታው ከተዘጋ በኋላ የሚቀርብ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።

*        ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታ ራሱን ማግለል አይቻልም።

*        የተጫራቾችን አድራሻ የሚገልፅ ሙሉ መረጃ ከሰነዱ ጋር መያያዝ አለበት።

*        መስሪያ ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

*        ተጫራቾች የውል ማስከበሪያ ካሽነፈው ዕቃ ከጠቅላላ ዋጋ 10% በባንከ የተረጋገጠ /cpo/ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

*        ተጫራቾች የቢሮ መስተንግዶ ላይ የምትወዳደሩ የውሃና የቆሎ ሳምፕል ማቅረብ አለባችሁ። ሳምፕል ያላቀረበ ተጫራች ድርጅት ከጨረታ ውጭ ይሆናል።

*        አሸናፊ ተጫራች ድርጅት የአሸነፋችሁትን ዕቃ በራሳችሁ ትራንስፖርት በማጓጓዝ ማቅረብ አለባችሁ።

አድራሻ፡- ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጳውሎስ ቅርንጫፍ ወደ አበበ ቢቂላ ስታዲየም መውረጃ 300 ሜትር ገባ ብሎ ይገኛል፡።

ለበለጠ መረጃ፦ ስልክ ቁጥር 011-230-6998 / 09 27 60 26 30/

ማሳሰቢያ፡-

-       በተጫረታችሁበት ዕቃ ላይ ዋጋ ስታስገቡ ቫትን ያካተተ መሆን ይጠበቅብዎታል መወዳደር የሚቻለው ንግድ ፍቃዱ ላይ በተሰጠው ስራ ዘርፍ ብቻ ነው።

-       ተጫራቾች ያስገባችሁትን ሳምፕል በቂ ማስቀመጫ ቦታ ስለሌለን አሸናፊና ተሸናፊ ከተለየ በኋላ በ60 ስልሳ የስራ ቀናት ውስጥ እንድትወስዱ እያሳሰብን በተቀመጠው ቀናቶች ውስጥ የማይወስድ ተጫራች ጽ/ቤቱ መስሪያ ቤቱ ሃላፊነቱን አይወስድም።

-       ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዛችሁትን cpo ለውል ማስከበሪያ ማዞር ማስያዝ አይቻልም።

-       ተጫራቾች ዋና የጨረታ ሰነድ ላይ ክፍል 2/ሁለት/ እና ክፍል 6/ስድስት/ በተጫራቾች የሚሞላውን ቅጽ መሙላት እና በየአንድአንዱ ገጽ ላይ ፊርማና የድርጅታችሁን ማህተም በማድረግ የጨረታ ሰነዱን መመለስ ይኖርባችኋል። ነገር ግን ከፍል 2 እና ክፍል 6 ላይ በተጫራቾች የሚሞላውን ቅፅ ያልሞላ ተጫራች እና

-       የጨረታ ሰነዱን ካልመለሰ /ተመላሽ ካላደረገ ከላይ የተጠቀሱትን ያላሟላ ተጫራች ጨረታው ውድቅ ይሆንበታል።

-       ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያም ሆነ ለውል ማስከበሪያ የምታሲዙት በCPO ብቻ ነው። ከሲፒኦ ውጪ በቼክና በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አይቻልም። ካስያዛችሁም ከውድድር ውጪ ትሆናላችሁ።

 

 

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት

✨ messages.ai_summary
Open tender for procurement of goods and services across 12 lots, including uniforms, office supplies, cleaning items, furniture, vehicle rental, printing, tailoring, agricultural seeds, and labor. Bidders must have valid licenses and tax IDs.
Save Tender