በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በምስራቅ ባሌ ዞን የራይቱ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት (በ2019ዓ.ም ጽ/ቤት በወረዳው ለሚገኙ ባለበጀት መ/ቤቶች አላቂ የቢሮ ዕቃዎች፣ የጽህፈት መሳሪያዎች፣ የጽዳት ዕቃዎች፣ ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች፣ ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችና የሰራተኞች ደንብ ልብስ በግልጽ ጨረታ ተጫራቶችን አወዳድሮ ካሸናፊው ላይ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በምስራቅ ባሌ ዞን የራይቱ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት (በ2019ዓ.ም ጽ/ቤት በወረዳው ለሚገኙ ባለበጀት መ/ቤቶች አላቂ የቢሮ ዕቃዎች፣ የጽህፈት መሳሪያዎች፣ የጽዳት ዕቃዎች፣ ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች፣ ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችና የሰራተኞች ደንብ ልብስ በግልጽ ጨረታ ተጫራቶችን አወዳድሮ ካሸናፊው ላይ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ ተጫራቶች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች እማልታችሁ በጨረታው እንድትሳተፉ እንጠይቃለን፡፡
- ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ዕቃ በዘርፉ የተሰማሩ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፤ የግብር መለያ ቁጥር (ቲን ነምበር) ያላቸውና የአቅራቢነት ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ቫት /VAT/ ያተመዘገበ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- CPO 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ብር የያዘ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ብቻ ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 1000 በመክፈል ራይቱ ወረዳ ገቢዎች ባለስልጣን ጽ/ቤት ከፍል ቢሮ ቁጥር 01 መግዛት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት በ16ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ተዘግቶ 3፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- የጨረታው መክፈቻ ቀን በዓል ወይም ዝግ ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን ጨረታው ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ሰነዱ ላይ ስማቸውን ሙሉ አድራሻቸውን ጽፈው ስርዝ ድልዝ ሳይኖረው ፈርመው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ሰነድ ዋናውንና ኮፒውን በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚያሸንፉትን ዕቃ ሙሉ በሙሉ መ/ቤቱ ግምጃ ቤት ድረስ በራሳቸው ወጪ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- አሸናፊው ላሸነፋባቸው ዕቃዎች ጠቅላላ ካሸነፈው ዋጋ ላይ 10% በጥሬ ብር ወይም በ/CPO/ (performance bond) ማስያዝ ይኖርበታል፡፡ ለውል ማስከበሪያ በዋስትና የተያዘው ብር ወይም /CPO/ ሙሉ መፈጸሙ እስኪረጋገጥ ድረስ ተይዞ ይቆያል፡፡
- ተጫራቾች ሰነዱ ላይ የተዘረዘሩትን ዕቃዎች በተሰጠው መግለጫ ቦታ ላይ የሚያቀርቡትን የዕቃ ስምና የተመረተበትን ሀገር /Brand name/ መግለጽ ይኖርባቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር /0914022218/0973156828/0912234296
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በምስራቅ ባሌ ዞን የራይቱ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
✨ messages.ai_summary
Open tender for supply of office furniture, stationery, cleaning supplies, electronics, and staff uniforms to budget offices in Raytu District, East Bale Zone, Oromia. Bidders need valid trade license, tax clearance, VAT registration, and supplier certificate.
