በቦሌ ከፍለ ከተማ የወረዳ 06 አስተዳደር ለ2019ዓ.ም ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ እቃዎችን መግዛት ይፈልጋል ፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቁጥር 001/18
በቦሌ ከፍለ ከተማ የወረዳ 06 አስተዳደር ለ2019ዓ.ም ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ እቃዎችን መግዛት ይፈልጋል ፡፡
- አላቂ የቢሮ እቃ/የፅሕፈት እቃዎች
- አላቂ የፅዳት እቃዎች
- ደንብ ልብስ
- ቋሚ እቃዎች
- የመኪና መለዋወጫ እቃዎች
- ህትመት ስራዎች(ውጤቶች)
- ትራንስፖርት አገልግሎት
- የጥገና አገልግሎት
- የመስተንግዶ አገልግሎት
ስለዚህ በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ድርጅቶች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባችኋል፡፡
- ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ ፡፡
- የመንግስት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ባዘጋጀው የእቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ፡፡
- ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር አስገቢው ባለስልጣን የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
- ለተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በየሎቱ 2% ማለትም
| ሎት | የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና cpo በብር |
| ሎት1 | 20,000 |
| ሎት2 | 30,000 |
| ሎት3 | 40,000 |
| ሎት4 | 40,000 |
| ሎት5 | 20,000 |
| ሎት6 | 20,000 |
| ሎት7 | 15,000 |
| ሎት8 | 15,000 |
| ሎት9 | 10,000 |
- ማንኛውም ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200/ሁለት መቶ ብር/በየሎቱ በመግዛት ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር ፋ/ፅ/ቤት 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 14 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን በታሸገ ኢንቨሎፕ ዘወትር በስራ ሰዓት ከ2፡30 እስከ 11፡00 ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል :: ጨረታው በ11ኛው ቀን 4፡00 ታሽጎ በዕለቱ በዛው ቀን 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ የጨረታው መዝጊያና መከፈቻ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተሰጠው ተመሳሳይ ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- የጨረታ አሸናፊ ከሆኑ ላሸነፉበት እቃ ዋስትና ወይም የውል ማስከበሪያ CPO 10% ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
- በተጨማሪ መስሪያ ቤቱ የጨረታውን 20% መቀነስ ወይም መጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው::
- ተጫራቾች ለመጫረት ሲመጡ ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ናሙና የማይቀርብባቸው ቋሚ ዕቃዎች መስሪያ ቤቱ ባቀረበው ስፔስፍኬሽን መሰረት ማቅረብ አለባቸው፡፡
- በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በመ/ቤቱ ግ/የስራ ሂደት ክፍል ድረስ በአካል ወይም በስልክ ቁጥር 0118678129 በመደወል ማግኘት ይችላሉ ፡፡
አድራሻ ፡- መገናኛ ወደ ጉርድ ሾላ በሚወስደው መንገድ ገባ ብሎ ውሃ እና ፍሳሽ ባስስልጣን ዋና መሥሪያቤት ፊትስፌት
በቦሌ ክፍስ ከተማ የወረዳ 06 ፋይናንስ ጽ/ቤት
✨ messages.ai_summary
Open tender for procurement of office supplies, cleaning materials, uniforms, fixed assets, vehicle spare parts, printing, transport, maintenance, and hospitality services. Bidders must hold valid licenses, be registered VAT taxpayers, and be listed on the government supplier registry.
