Tender Detail

Tender Details


የሀላባ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በሀላባ ዞን ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች ለ2018 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውል አላቂና ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች ግዥ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡


 

የጨረታ ማስታወቂያ

 

የሀላባ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በሀላባ ዞን ለሚገኙ ሴክተር /ቤቶች 2018 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውል አላቂና ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች ግዥ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህ መሠረት

  1. ሎት1 አላቂ እና ሌሎች አላቂ እቃዎች
  2. ሎት2 የደንብ ልብስ
  3. ሎት3 ኤሌክትሮኒ
  4. ሎት4 ፈርኒቸር
  5. ሎት5 ሞተር ሳይ
  6. የህትመት ሥራ (ባነር፣ ባጅ፣ መታወቂያ፣ የቢሮ ማህተሞች፣ የኃላፊ የስም ቲተር፣ ሰርተፊኬት)
  7. የሀላባ የባህል አልባሳት የወንድና የሴት
  8. እስታንዳርዱ የጠበቀ የቢሮ መጋረጃ
  9. የመብራት እቃዎች
  10. የተለያዩ የፈረስ ጉልበት ያላቸው ጀነሬተሮች ስለዚህ
  1. ተጫራቾች አግባብነት ያለው በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፍቃድ፣ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት የተጨማሪ እሴት ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (Tin) ሰርተፊኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ( ሊራንስ) ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ እንዲሁም በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ መመዝገብ ይኖርባቸዋል፡፡ እንዲሁም ተጨማሪ መቅረብ ያለባቸው ሰነዶች በጨረታ ሰነዱ በተገለፀው መሠረት ይሆናል፡፡
  2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት 21 ተከታታይ የስራ ቀን ውስጥ የጨረታ ሰነዱን እያንዳንዱን በብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመግዛት መውሰድ ትችላላችሁ
  3. ጨረታው 22ተኛ ቀን የጨረታው ሳጥን 400 ሰዓት ታሽጎ 430 ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ይሆናል ሆኖም ግን በመፈቻው ቀን የተጫራቾች ያለመገኘት መምሪያው ጨረታውን ከመፈት የሚያስተጓጉለው ነገር አይኖርም፡፡
  4. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ለእያንዳንዱ ሎት ብር 5000 /አምስት ሺህ ብር/ በባንክ ዋስትና በታወቀ ባንክ የተረጋገጠ ፍያ ማዘዣ (CPO) ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
  5. የጨረታው አሸናፊ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ 10% የውል ማስከበሪያ (CPO) ወይንም ንኮንዲሽናል ባንከ ጋራንት ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
  6. የጨረታው ፈቻ ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በቀጣይ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ጨረታው የሚከፈት ይሆናል፡፡
  7. መምሪያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው

 

የሀላባ ዞን ፋይናንስ መምሪያ

ሀላባ ቁሊቶ

 

Save Tender