Tender Detail

Tender Details


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን ከታች የተገለጹትን ነገሮች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት እና ለማሰራት ይፈልጋል።


 

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር 05

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን ከታች የተገለጹትን

ሎት 1 :- የጽህፈት መሳሪያዎች እና የፎቶ ኮፒ የፕሪንተር ቀለሞች ለመግዛት፤

ሎት 2 :- የደንብ ልብሶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት፣

ሎት 3 :- የጽዳት እቃዎች ለመግዛት፤

ሎት 4 :- የኤሌክትሪክ፣ የቧንቧ፣ የግንባታ እቃዎች ለመግዛት፣

ሎት 5 - የመኪና ጎማዎች ለመግዛት፣

ሎት 6- የመኪና ኪራይ 2018 በጀት አመት፣

ሉት 7 :- የተለያዩ የችግኝ ዝግጅት ግብአቶች እና እቃዎች ለመግዛት፣

ሎት 8 :- የባነር እና የብሮ ህትመት እና የተለያዩ ህትመቶች ለአንድ አመት ውል በማሰር ለማሰራት፣

ሎት 9 - የአትክልትና ፍራፍሬ ለአንድ አመት ውል በማሰር ለመግዛት፤

ሉት 10 - የሆቴል ምግብና መጠጥ አቅርቦት አገልግሎት የአንድ አመት ውል በማሰር ለመግዛት፣

ሎት 11 :- የበሬ ስጋ አቅርቦት ለአንድ አመት ውል በማሰር ለመግዛት፣

ሎት 12 :- ፋውንቴኖችን ፣የውሃ ፓምፖችን የጀኔሬተር፣ የሳር ማጨጃ ማሽን ውል በማሰር ሰርቪስ የማድረግ ስራ ለማሰራት፣

ሎት 13- በኮርፖሬሽኑ ፓርክ ውስጥ የሚገኙ ህንጻዎችና የቢሮ እቃዎች እና መጫወቻዎች የጥገና ስራ ውል በማሰር ለማሰራት፣

ሎት 14- ለእንስሳት መድሀኒቶች ቋሚ እቃዎች ለመግዛት፣

ሉት 15- የስብሰባ አዳራሽ ጠረ ለመግዛት፣

ሎት 16- የጉልበት ለአንድ አመት ውል በማሰር ለማሰራት፣

ሎት 17- የኮምፒዩተር፣ ላፕቶፕ፣ ፕሪንተር እና ፎቶ ኮፒ ጥገና አገልግሎት የሚሰጥ ድርጅት ለአንድ አመት ውል በማሰር ለማሰራት

በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። በመሆኑም የተጠቀሱትን መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቶች ተጋብዘዋል።

  1. ተጫራቾች በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስ ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፍኬት እና ስለግብር አከፋፈል የሚሰጥ ማስረጃ (clearance) ማቅረብ አለባቸው
  2. ተጫራቾች ሁሉም ሎቶች ለእያንዳንዳቸው 30,000.00 (ሰላሳ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሲፒኦ ወይም ባንክ ጋራንቲ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን ስም ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  3. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 500 /አምስት መቶ ብር/ መገኛኛ ዘፍመሽ ፊት ለፊት ታሜጋዝ ህንጻ ሁለተኛ ፎቅ ላይ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአስር ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ከጠዋት 230 እስከ 1130 ሰዓት ድረስ በመቅረብ መግዛት ይቻላል።
  4. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ፋይናንሻል ዶክመንት ለብቻ እና ቴክኒካል ዶክመንት ለብቻ በማሸግ እና ሁለቱንም ለየብቻ ኮፒ በማድረግ በፖስታ በማሸግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሳጥኑ እስከሚታሸግበት 10ኛው ተከታታይ የስራ ቀን በኋላ 11ኛው ቀን ከሰአት 800 ድረስ ለዚህ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
  5. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 11ኛው የስራ ቀን 800 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ በዚያው ቀን 830 መገኛኛ ዘፍመሽ ፊት ለፊት ታሜጋዝ ህንጻ ስድስተኛ ፎቅ የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል።
  6. የጨረታ መክፈቻው ቀን ቅዳሜና እሁድ ላይ የሚውል ከሆነ በቀጣዩ ሰኞ በተጠቀሰው ሰዓት ተዘግቶ የሚከፈት ይሆናል።
  7. ዘግይቶ የደረሰ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
  8. ኮርፖሬሽኑ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

ተጨማሪ መረጃ፡- ስልክ ቁጥር 0703229872 / 251777619010 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን

 

Save Tender