በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ሆሳዕና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከመደበኛ ከካፒታል እና ከውስጥ ገቢ በ2018 በጀት ዓመት ላይ የሥልጠና ዕቃ መግዛት ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ሆሳዕና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከመደበኛ ከካፒታል እና ከውስጥ ገቢ በ2018 በጀት ዓመት ላይ የሥልጠና ዕቃ መግዛት ይፈልጋል።
ሎት 01 የጽህፈት መሳሪያ ሎት 08 ኤሌክትሪክ እና ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች
ሎት 02 የኮምፒውተር ዕቃዎች ሎት 09 ሆቴል ማኔጅመንት ዕቃዎች
ሎት 03 ሰርቨይንግ እና የካድስትራል ዕቃዎች ሎት 10 አርባንጊሪን ዕቃዎች
ሎት 04 ጋርመንት ዕቃዎች ሎት 11 የቢሮ ውበት የፅዳት ዕቃዎች
ሎት 05 ብረታ ብረት ዕቃዎች ሎት 12 ኮንስትራክሽን ዕቃዎች
ሎት 06 አውቶሞቲቭ ዕቃዎች ሎት 13 ወተር ሰፕላይ እና ሳንቴሽን ዕቃዎች
ሎት 07 ፈርኒቸር እና የቢሮ ዕቃዎች ሎት 14 የደንብ ልብስ
ማሳሰቢያ፡ በዘርፉ ወይም በንግድ ሥራ መስኩ የተሰማሩ መሆኑን የሚገልፅ የታደሠ የንግድ ፈቃድ እና የዘመኑን ግብር መክፈላቸውን የሚያረጋግጥ በግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ ማስረጃ እንዲሁም የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ፡፡
1ኛ. ተጫራቾች በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ያላቸው።
2ኛ. የግዥው መጠን ብር 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ ተጨማሪ እሴት ታክስ (vat) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
3ኛ. ለተጠቀሰው ጨረታ የማይመሰለ ለእያንዳንዱ ሎት 300 /ሶስት መቶ ብር ብቻ/ በኮሌጁ የውስጥ ገቢ አካውንት ቁጥር 1000021271385 ላይ ገቢ በማድረግ የተዘጋጀውን የጨረታ ዝርዝር ሠነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 /ለአስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት የእረፍት ቀናትና በዓላትን በመጨመር ከአዲስ አበባ ተግባረዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ ውስጥ እና ከሆሳዕና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቢሮ ቁጥር 27 ከግዥ ቡድን መግዛት ይችላሉ፡፡
4ኛ. ተጫራቾች የሚወዳደሩበት ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ኦርጅናል እና ሁለት ኮፒ ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ16 ለአሥራ ስድስት ተከታታይ የሥራ ቀናት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
5ኛ. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በወጣበት በ16ተኛ አስራ ስድስተኛ ቀን በ9:00 ተዘግቶ የሚከፈተውም በተዘጋበት ዕለት 9፡30 ሰዓት ከአዲስ አበባ ተግባረዕድ ፖሊ ቴከኒክ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ ውስጥ እና ከሆሳዕና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቢሮ ቁጥር 27 የጨረታ ኮሚቴዎች አባላት እና ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይሆናል፡፡
6ኛ. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
7ኛ. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለእያንዳንዱ ሎት 5000.00 /አምስት ሺህ ብር ብቻ/ በባንክ የተረጋገጠ የከፍያ ትዕዛዝ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው።
8ኛ. ተጫራቾች ያሸነፈባቸውን ዕቃዎች በማጓጓዝ ሆሳዕና ፖሊ ቴክኒከ ኮሌጅ ስቶር ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
9ኛ. በጨረታ አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ያሸነፈባቸውን ዕቃዎች ውል ማስከበሪያ 10% በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው
10ኛ. ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0465551997/0912711177ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
ሆሳዕና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
