Tender Detail


የወላይታ ሶዶ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም ለአንደኛ ዙር የተለያዩ የስልጠና ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አውዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡


 

የጨረታ ማስታወቂያ

 

የወላይታ ሶዶ ፖሊቴኒክ ኮሌጅ 2018 . ለአንደኛ ዙር የተለያዩ የስልጠና ዕቃዎችን ማለትም፡-

ሆቴልና ቱሪዝም ዕቃ                             የቧንቧና ውሃ ሥራ ዕቃ

አግሮ ፕሮሰሲንግ ዕቃ                            የቅየሳ Seurveying/ ሥልጠና ዕቃ

ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒስ                    የከተማ ውበት /Urban greenery ዕቃ

አውቶሞቲቭ ዕቃ                                ቆዳና የቆዳ ውጤቶችን /ሌዘ

ማኑፋቸሪንግ/ብረታ-ብረት                    ሳኒተሪ ዕቃዎች

እንጨትና የእንጨት ሥራ                        የቤትና ቢሮ/ፈርኒቸር ዕቃዎች

የአይሲቲ ኮምፒተር ዕቃዎች

የጽህፈት መሣርያዎች

የጽዳት ዕቃዎችን

ጋርመንት አልባሳት/ደንብ ልብስ በግልጽ ጨረታ አውዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

ኮንስትራከሽንና ሮድ ኮንስትራክሽን ዕቃዎች

ሆነም ተጫራቾች፡-

  • የዘመኑን የታደሰ የንግድ ፈቃድና የንግድ ምዝገባ ምስ ወረቀት ማቅረብ የሚችል፤
  • የግብር ከፋይነት መለያ (VAT) ሰርተፍኬት ያለው፣
  • በአቅራቢነት የተመዘገበበትን መረጃ/የድረ- ገጽ ምዝገባ ሰነድ ማቅረብ የሚችል
  • የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የዘመኑን የግብር ግዴታዎችን ስለመወጣታቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ሆኖ ከዚህ በታች በተዘረዘረው መሰረት ማለትም፡-
  • የእያንዳንዱን ጨረታ ነድ መግዣ የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ ብቻ በመፈል ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 የስራ ቀናት ውስጥ ወላይታ ሶዶ ፖሊ /ኮሌጅ ቢሮ ቁጥር 104 በመምጣት የጨረታ ሰነዱን በመግዛትና ኮሌጁ ባዘጋጀው ጨረታ ሰነድ ሞልተው በማስገባት መወዳደር ይቻላል፡፡
  • ጨረታው በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ 2ኮፒ በጨረታ ሳጥኑ መጨመር ያለበት ሲሆን ከአንድ በላይ የጨረታ ሰነድ የሚገዙ ድርጅቶች ሲፒኦን በጥቅል ማድረግ ሲችሉ ሌሎች ሰነዶችን በእያንዳንዱ ፖስታ ውስጥ ከጨረታ ሰነድ ጋር ካላሽጉ ከጨረታው ውጪ ይደረጋሉ።
  • ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዕቃዎች ጠቅላላ ዋጋ 1% የጨረታ ማስከበሪያ በማስላት በባን የተረጋገጠ ቼክ ጋራንት እና ሲፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ የጠቅላላ ዋጋ 1% በታች የሚያስገቡ ተጫራቾች ከጨረታ ውጪ ይደረጋሉ፡፡ አሸናፊዎች በቅድሚያ 10% ውል በመግባት የውል ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ በማስያዝ ውል ይገባሉ፡፡ አሸናፊ ድርጅቶች ውል ለመግባት ፈቃደኛ ካልሆኑ የጨረታ ማስከበሪያው ውርስ ይደረጋል።
  • ኮሌጁ ከአሸናፊ ድርጅቶች ያሸነፉትን ዕቃ የሚረከበው ውል ከገቡበት ቀን ጀምሮ በኮሌጁ ግቢ ብቻ ስለሆነ ጨረታውን የሚያሸንፉ ድርጅቶች ያሸነፉትን ሙሉ ዕቃ እስከ ኮሌጁ ግቢ በማምጣት የሚያስረከቡ ይሆናሉየዕቃዎቹም ጥራትና ዓይነት በኮሌጁ ባለሙያዎች ተረጋግጦ ተቀባይነት ካላገኘ ኮሌጁ ለመረከብ አይገደድም
  • ጨረታው የሚታሸግበት ቀንና ቦታ፡- ሶዶ ፖሊቴ ኮሌጅ ግቢ ሲሆን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 15ኛው የስራ ቀን ከቀኑ 1030 ሰዓት ሲሆን 15ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይሆናል፡፡
  • የሚከፈትበት ቀንና ቦታ ወላይታ ሶዶ ፖሊቴ ኮሌጅ ግቢ የጨረታ ሰነዱ ተሸጦ በተጠናቀቀበት 2ኛው የስራ ቀን ከቀኑ 400 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል
  • ተሸናፊ ድርጅቶች ያስያዙት ሲፒኦ ይመለስላቸዋል፡፡
  • በጨረታ ሰነድ ላይ የተገለጸውን ስፔስፒከሽን መቀየርና መደለዝ እንዲሁም የተደለዘ የተጫራች ሰነድ ተጫራቾችን ከጨረታው ውጪ ያደርጋቸዋል
  • ድርጅቶች ተገቢውን አድራሻ ማህተም ስል እና የፋክስ ቁጥርን ጨምሮ በሰነዱ መግለጽ ይኖርባቸዋል።
  • ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኝ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመስረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

መረጃ በስልክ ቁጥር:- 0912111340 /0913302499/ 0916715114 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡

 

የወላይታ ሶዶ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

ወላይታ ሶዶ

 

Save Tender