በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2018 በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን እቃዎች አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር አ/አ/ደ/ማ/ባ/እቃ/ግ/ጨ/04/2018
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2018 በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን እቃዎች አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
|
ሎት ቁጥር |
የሚገዛው የእቃ ዓይነት |
የጨረታ ማስከበሪያ (CPO) መጠን |
ምርመራ |
|
1 |
አላቂ የቢሮ እቃዎች |
15,000.00 |
|
|
2 |
ቋሚ አላቂ እቃዎች |
5,000.00 |
|
|
3 |
የቢሮ የሻይና ቡና እቃዎች የቡና ስኒ፣ የሻይ ብርጭቆ ወዘተ |
8,000.00 |
|
|
4 |
ለዴይ ኬር አገልግሎት የሚውሉ እቃዎች |
4,000.00 |
|
|
5 |
የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች |
50,000.00 |
|
|
6 |
መስተንግዶ ቡና ቆሎ፣ ኩኪስ ወዘተ |
25,000.00 |
|
|
7 |
የቢሮ ሰራተኞች የደንብ ልብስ |
25,000.00 |
|
|
8 |
የአሉሚኒም በር ተንጠልጣይ ቁልፍ እና ጥገና አገልግሎት |
30,000.00 |
|
|
9 |
የመድረክ ዝግጅት አገልግሎት በጥቅል |
10,000.00 |
|
|
10 |
የፓራሚሊተሪ ኦፊሰር ካልሲ |
100,000.00 |
|
|
11 |
የሰራተኞች የካፊቴሪያ አገልግሎት |
የቤት ካርታ ወይም የመኪና ሊብሬ |
|
|
12 |
የተፈጥሮ አበባ እና አርቲፊሻል አበባ |
30,000.00 |
|
|
13 |
የፈርኒቸር እቃዎች |
30,000.00 |
|
|
14 |
የጂም እቃዎች ሎት 14 |
50,000.00 |
|
በዚህ መሰረት በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መመሪያዎች በማሟላት መወዳደር ይችላሉ፡-
- በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ ስለመሆናቸው የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
- የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው፤
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ቲን TIN ማቅረብ የሚችሉ
- የአቅራቢነት ምዝገባ ሰነድ ማቅረብ የሚችሉ፤
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው ቀን ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ ከ2፡30 – 11፡00 ሰዓት ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት 8ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 08/15 በመቅረብ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ቴክኒካል ኦርጅናል እና ኮፒ እንዲሁም ፋይናንሻል ኦርጅናልና ኮፒ በታሸገ ኤንቨሎፕ ለየብቻው በማቅረብ ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 /አስር/ ተከታታይ የስራ ቀናት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ግዥና ንብረት አ/ጠ/አ/ዳይሬክቶሬት 9ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 09/22 / ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፤
- የሚቀርበው ዋጋ ማቅረቢያ ፊርማና ማህተም ከሌለው ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ናሙና የተጠየቀባቸው እቃዎች ጨረታው 88 ከመከፈቱ በፊት የድርጅታቸውን ማህተም በማድረግ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ጨረታው በ11ኛው ቀን በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 3፡30 ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻው በተገኙበት 4፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች በሚጫረቱበት እያንዳንዱ እቃ ጥራት በቴክኒክ ብቃታቸው ከተመረጡ በዋጋ የሚወዳደሩ ይሆናል፡፡
- ጨረታው ከተዘጋ በኋላ የሚቀርቡት የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብት የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- አ/አ አራዳ ክፍል ከተማ (ፒያሳ) ልዩ ስሙ እሪ በከንቱ ተብሎ በሚጠራው የኢትዮጵያ ስታቲስቲካል አገልግሎት ቢሮ አካባቢ እስጢፋኖስ መካሻ አማረ (EMA) ህንፃ 9ኛ ፎቅ፣ ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0115622843 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን
